የኮሚሽነር አበረ አዳሙ የቀብር ሥርዓት ተፈጸመ

የኮሎኔል አዳሙ አበረ ሥርዓተ ቀብር

ቀብራቸው በባሕር ዳር ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል

ኢዛ (ሐሙስ ሚያዝያ ፳፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 6, 2021)፦ በድንገተኛ ሕመም መሞታቸው የተነገረው የአማራ ክልል የቀድሞ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አበረ አዳሙ የቀብር ሥርዓታቸው ዛሬ ሐሙስ ሚያዝያ 28 ቀን 2013 ዓ.ም. በባሕር ዳር ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዶክተር ሙሉ ነጋ ወደቀደመው ሚኒስትር ዴኤታነታቸው ተመልሰዋል

Mulu Nega (PHD)

ትናንት ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚነታቸው ተነስተዋል

ኢዛ (ሐሙስ ሚያዝያ ፳፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 6, 2021)፦ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚነታቸው የተነሱት ዶክተር ሙሉ ነጋ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ከመሾማቸው ከኅዳር 4 2013 ዓ.ም. ጀምሮ በፊት ወደነበሩበት የኃላፊነት ቦታ ላይ በድጋሚ ተሹመዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዶክተር ሙሉ ነጋ ትግራይን ከማስተዳደር ኃላፊነታቸው ተነሱ

ዶ/ር አብርሃም በላይ

ዶ/ር አብርሃም በላይ ሥልጣኑን ተረክበዋል

ኢዛ (ረቡዕ ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 5, 2021)፦ ባለፉት ስድስት ወራት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመኾን ሲያገለግሉ በነበሩት ዶ/ር ሙሉ ነጋ ምትክ ዶ/ር አብርሃም በላይ መሾማቸው ተነገረ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“የሱዳን ድፍረት ቅጥ አጥቷል” ኢትዮጵያ

ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል

የህዳሴ ግድብ የሚገኝበትን የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሱዳን ይገባኛል ላለችው፤ ኢትዮጵያ ምላሽ ሰጠች

ኢዛ (ማክሰኞ ሚያዝያ ፳፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 4, 2021)፦ የሱዳን መንግሥት ከወራት በፊት በኃይል የያዘችው የኢትዮጵያ መሬት ሳያንስ፤ አሁን ደግሞ ታላቁ የህዳሴ ግድብ የሚገኝበትን የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልልን ይገባኛል ማለትዋ ሱዳን ቅጥ ያጣችና ልክ እያለፈች መኾኑን የሚያሳይ ነው ሲል የኢትዮጵያ መንግሥት ገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“አርበኞቻችን እንደነበሩበት ዘመን ዛሬም ኢትዮጵያ በውስጥ ባንዳዎችና በውጭ ጠላቶች ሙከራ እየተቃጣባት ነው”

 የአርበኞች ቀን

"አሁን በኢትዮጵያ ላይ እየተቃጣ ያለውን ለኢትዮጵያ የሚደገስ የመከራ ድግስ መቀልበስ የሚቻለው ከተቀናጀን፣ ከተባበርን፣ ከተናበብን ነው" ጠ/ሚ/ር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ

ኢዛ (ማክሰኞ ሚያዝያ ፳፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 4, 2021)፦ አርበኞቻችን እንደነበሩበት ዘመን ዛሬም ኢትዮጵያ በውስጥ ባንዳዎችና በውጭ ጠላቶች ሙከራ እየተቃጣባት መኾኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር የነበሩት አበረ አዳሙ አረፉ

አበረ አዳሙ

ሕይወታቸው ያለፈው በሕክምና ተቋም ውስጥ መኾኑ ተነገረ

ኢዛ (ማክሰኞ ሚያዝያ ፳፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 4, 2021)፦ ከሳምንት በፊት ሚያዝያ 19 ቀን ከአማራ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር የነበሩት አበረ አዳሙ ከዚህ ዓለም መለየታቸው ታወቀ። የክልሉ መንግሥት በድንገተኛ ሕመም ምክንያት የሕክምና እርዳታ ሲደረግላቸው መቆየቱንና ሕይወታቸው ማለፉን ገልጿል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአውሮፓ ሕብረትና የኢትዮጵያ ፍጥጫ

European Union Flag

ሕብረቱ ምርጫውን አልታዘብም ሲል
ኢትዮጵያ ሕብረቱ ሉዓላዊነትን የሚጋፋ ጥያቄ በማቅረቡ ትከሳለች
በምርጫው ታዛቢ ላለመላክ የተፈለገውም ኢትዮጵያ ሉዓላዊነቴን የሚጋፋ አካሔድ አልቀበልም በማለቷ ነው

ኢዛ (ማክሰኞ ሚያዝያ ፳፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 4, 2021)፦ የአውሮፓ ሕብረት በኢትዮጵያ የሚካሔደውን አገር አቀፍ ምርጫ 2013 ታዛቢዎቹን እንደማይልክ አስታወቀ። ውሳኔውን የኢትዮጵያ መንግሥት ያልተገባ ብሎታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀድሞ ኢሜይል ሃክ ተደረገ?

PM Abiy Ahmed

ወንጀለኞች በቀድሞ ኢሜላቸው ሐሰተኛ መረጃ እያሰራጩ በመኾኑ ጥንቃቄ አድርጉ ተባለ

ኢዛ (ማክሰኞ ሚያዝያ ፳፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 4, 2021)፦ በቀድሞ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የግል ኢሜይል አድራሻ የተላከ በማስመሰል እየተሰራጨ ያለ መረጃ እንዳለ በመግለጽ፤ ጥንቃቄ እንዲደረግ የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በሕወሓት እና ኦነግ ሸኔ ላይ በሽብርተኝነት እንዲፈረጁ የቀረበው የውሳኔ ሐሳብ ላይ ተቃውሞ ላላቸው የ48 ሰዓት ተሰጠ

ፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ

ይህ የ48 ሰዓታት ማስታወቂያ የወጣው ለመጀመሪያ ጊዜ መኾኑ ነው

ኢዛ (ሰኞ ሚያዝያ ፳፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 3, 2021)፦ ሕወሓት እና ኦነግ ሸኔ በሽብርተኝነት እንዲሰየሙ በቀረበው የውሳኔ ሐሳብ ላይ ተቃውሞ ያላቸው በ48 ሰዓት ውስጥ ማስረጃቸውን እንዲያቀርቡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስታወቀ። ይህ የ48 ሰዓታት ማስታወቂያ የወጣው ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ ከ80 ዓመት በኋላ የውጭ ወረራ ሊቃጣባት ስለሚችል ኢትዮጵያውያን በአንድ እንዲቆሙ ጠየቀ

ልጅ ዳንኤል ጆቴ

“የውጭና የአገር ውስጥ ጠላቶ ቢተባበሩም ኢትዮጵያን ሊያቆስሏት ይችላሉ እንጂ፤ አያሸንፏትም” ልጅ ዳንኤል ጆቴ

ኢዛ (ሰኞ ሚያዝያ ፳፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 3, 2021)፦ ከነገ በስቲያ ረቡዕ ሚያዝያ 27 ቀን 2013 ዓ.ም. 80ኛ ዓመት የድል በዓልን (የአርበኞች ቀን) አስመልክቶ ዛሬ መግለጫ የሰጡት የጥንታዊት ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ፕሬዝዳንት ኢትዮጵያ ከሰማንያ ዓመት በፊት የገጠማት የውጭ ወረራ የሚመስል ችግር እየገጠማት በመኾኑ ኢትዮጵያውያን በአንድነት ይቁሙ አሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ