አነጋጋሪው የፓትርያርኩ መግለጫ ከቤተ ክርስቲያኗ እውቅና ውጭ እንደኾነ ተገለጸ

ሊቀ ጳጳስ አቡነ ዮሴፍ

“ፓትርያርኩ የሲኖዶሱን ይሁንታ ሳያገኙ መግለጫ መስጠት አይችሉም” አቡነ ዮሴፍ

ኢዛ (ሰኞ ግንቦት ፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 10, 2021)፦ ሰሞኑን አነጋጋሪ ኾኖ የሰነበተው ብፁዕ ወ ቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓርትሪያክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የሰጡት መግለጫ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ሳይኾን፤ የግላቸው መኾኑን አቡነ ዮሴፍ አስታወቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የተመዘገቡ የመራጮች ቁጥር 31.7 ሚሊዮን ደርሷል

National Election Board of Ethiopia (NEBE)

በአዲስ አበባ 1,212,073 ዜጎች ተመዝግበዋል

ኢዛ (ቅዳሜ ሚያዝያ ፴ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 8, 2021)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ቅዳሜ ሚያዝያ 30 ቀን 2013 ዓ.ም. ይፋ ባደረገው መረጃ ለስድስተኛው አገራዊ ምርጫ 2013 የተመዘገቡ የመራጮች ቁጥር 31,724,947 መድረሱን አስታወቀ። በአዲስ አበባ 1,212,073 ዜጎች ተመዝግበዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ምርጫ ቦርድ በሶማሌ ክልል ለተወሰኑ የምርጫ ክልሎች የመራጮች ምዝገባን በጊዜያዊነት አስቆመ

Somali region, Ethiopia

የምርጫ ክልሎቹ ያልተገባ ተግባራት የተፈጸመባቸው ናቸው ተብሏል

ኢዛ (ቅዳሜ ሚያዝያ ፴ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 8, 2021)፦ ከምርጫ ምዝገባ ጋር በተያያዘ ከፍተኛ አቤቱታ እየቀረበበት መኾኑ በተነገረለት በሶማሌ ክልል፤ በተወሰኑ የምርጫ ክልሎች ላይ የመራጮች ምዝገባ በጊዜያዊነት እንዲቆም የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ መወሰኑን አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዘጠኝ ፓርቲዎች የአውሮፓ ሕብረትን እርምጃ ኮነኑ

European Union Flag

የጋራ ምክር ቤቱ የአውሮፓ ሕብረት ጥያቄን ሉዓላዊነትን የሚጋፋ ብለውታል

ኢዛ (ቅዳሜ ሚያዝያ ፴ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 8, 2021)፦ በአማራ ክልል በምርጫ ጉዳዮች አብሮ ለመሥራት የጋራ ምርጫ ምክር ቤት ያቋቋሙት የአማራ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የአውሮፓ ሕብረት፤ ምርጫውን ለመታዘብ የኮምዩኒኬሽን መሣሪያ ይዤ ይግባ፣ ከምርጫ ቦርድ በፊት መግለጫ ልስጥ ብሎ ያቀረበው ጥያቄ የአገር ሉዓላዊነትን የሚጋፋ ነው አለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሞት ወደ ሕይወት

Commercial Bank of Ethiopia

ባንኩን ችግር ውስጥ ከከተቱት በርካታ ምክንያቶች መካከል ለመንግሥት የልማት ድርጅቶች በገፍ የተሰጠው ብድር አንዱ

ኢዛ (ቅዳሜ ሚያዝያ ፴ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 8, 2021)፦ በኢትዮጵያ ውስጥ ግዙፍ አሴት አላቸው ተብለው ከሚጠቀሱት መንግሥታዊ ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንዱ ነው። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአሁኑ ወቅተ ወደ አንድ ትሪሊዮን የሚጠጋ (938 ቢሊዮን ብር) አሴት ያለው ሲሆን፤ የአገሪቱ ትልቁ ባንክም ነው። ከባንክ ኢንዱስትሪው ወደ 65 በመቶ የሚኾነውን የገበያ ድርሻ የያዘም ነው። ይህ አንጋፋ ባንክ ሰማኒያኛ ዓመቱን ለማክበር ዋዜማ ላይ ያለ ሲሆን፤ ለአገራዊ ኢኮኖሚ ሲሰጥ የነበው ጠቀሜታ እጅግ ከፍተኛ ነው። እንደ ፖሊሲ ባንክ የሚታይ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአውሮፓ ሕብረት ነገር

Ambassador Dina Mufti

እንደገና ምርጫውን ለመታዘብ ፍላጎት አለኝ አለ

ኢዛ (ቅዳሜ ሚያዝያ ፴ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 8, 2021)፦ በኢትዮጵያ የሚካሔደውን ስድስተኛውን አገር አቀፍ ምርጫ 2013 ታዛቢዎቼን አልክም ብሎ አሳውቆ የነበረው የአውሮፓ ሕብረት፤ አሁን ደግሞ ምርጫውን የሚታዘቡ ኤክስፐርቶች እልካለሁ ማለቱ ተሰማ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለመራጭነት 28 ሚሊዮን ዜጎች ተመዝግበዋል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ (ምርጫ 2013)

የመራጮች ምዝገባ ለሁለተኛ ጊዜ ተራዘመ

ኢዛ (ዓርብ ሚያዝያ ፳፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 7, 2021)፦ በስድስተኛው አገራዊ ምርጫ 2013 እስካሁን የተመዘገቡ የመራጮች ቁጥር ከ28 ሚሊዮን በላይ መድረሱ ተገለጸ። የመራጮች ምዝገባ ለተጨማሪ ሰባት ቀናት (አንድ ሳምንት) እንዲራዘም መወሰኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ማዕድናት በምርት ገበያ በኩል ሊገበያዩ ነው

የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትር ኢንጂንየር ታከለ ኡማ እና አቶ ወንድማገኘሁ ነገራ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ

ምርቱን በጥራት በማምረት ለአገር ውስጥ እና ለዓለም አቀፍ ገበያዎች በስፋት ለማቅረብ ግብይቱን በዘመናዊ ሥርዓት ለማካሔድ ያስችላል ተብሏል

ኢዛ (ዓርብ ሚያዝያ ፳፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 7, 2021)፦ የአገሪቱ የከበሩ ማዕድናት በኢትዮጵያ የምርት ገበያ በኩል እንዲገበያዩ ለማድረግ የሚያስችል ስምምነት ዛሬ ተፈርሟል። ምርቱን በጥራት በማምረት ለአገር ውስጥ እና ለዓለም አቀፍ ገበያዎች በስፋት ለማቅረብ ግብይቱን በዘመናዊ ሥርዓት ለማካሔድ ያስችላል ተብሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ምርጫ ቦርድ ከእጩ መተካትና ተያያዥ ጥያቄዎችን ከዛሬ ጀምሮ እንደማያስተናግድ ገለጸ

Ethiopian Election 2021

እስከዛሬ የደረሱትን እንደሚያስተናግድና ለዚህም ምክንያቱ የድምፅ መስጫ ወረቀት ሕትመት ላይ በመኾኑ ነው ሲል አስታውቋል

ኢዛ (ሐሙስ ሚያዝያ ፳፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 6, 2021)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከዛሬ ሚያዝያ 28 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ የተወዳዳሪ እጩዎችን የመተካት፣ የመቀየር፣ የመለወጥ እና ማንኛውንም ዐይነት ተያያዥ ማሻሻያዎችን እንደማይቀበል አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኮሚሽነር አበረ አዳሙ የሕይወት ታሪክ

አበረ አዳሙ

ኮሚሽነር አበረ አዳሙ በጣም ቆፍጣና ወታደር፣ ምሁር፣ ደራሲ፣ ገጣሚ እና የሕግ ባለሙያ ሲኾኑ፤ ከሦስት በላይ ቋንቋዎችን አቀላጥፈው መናገርና መጻፍ የሚችሉ፣ በሁሉም ዘርፍ በሚባል ደረጃ ሙሉ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ነበሩ

አማራ ሚድያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) - ኮሚሽነር አበረ አዳሙ ከአባታቸው ከአቶ አዳሙ መኮንን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ጦቢያ ንጋቱ የካቲት 13 ቀን 1961 ዓ.ም. በቀድሞው የጎጃም ክፍለ አገር ቆላ ደጋ ዳሞት አውራጃ ደጋዳሞት ወረዳ መለስ ብሳና ሜዳ ቀበሌ ተወለዱ። ዕድሜያቸው ለትምህርት እስኪደርስ በቤተሰቦቻቸው እንክብካቤ አድገው በ1973 ዓ.ም ወይን ውኃ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገብተው እስከ 8ኛ ክፍል ተማሩ። ኮሚሽነር አበረ አዳሙ ባላቸው ትምህርትን የመቀበል ተፈጥሯዊ ተሰጥዖ በአራት ዓመታት ውስጥ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በማጠናቀቅ አገር አቀፉን የስምንተኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና ከፍተኛ ውጤት በማምጣት ወደ 9ኛ ክፍል ተዛውረዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ