Mulu Nega (PHD)

ዶክተር ሙሉ ነጋ

ትናንት ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚነታቸው ተነስተዋል

ኢዛ (ሐሙስ ሚያዝያ ፳፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 6, 2021)፦ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚነታቸው የተነሱት ዶክተር ሙሉ ነጋ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ከመሾማቸው ከኅዳር 4 2013 ዓ.ም. ጀምሮ በፊት ወደነበሩበት የኃላፊነት ቦታ ላይ በድጋሚ ተሹመዋል።

ዛሬ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የወጣው መረጃ ዶ/ር ሙሉ ነጋ የሣይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ በመኾን መሾማቸውን አስታውቋል።

ዶ/ር ሙሉ ከሚያዝያ 28 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ በሚኒስትር ዴኤታነት ወደሚሠሩበት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ሲመለሱ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚነታቸውን ደግሞ ለዶ/ር አብርሃም በላይ ያስረክባሉ። (ኢዛ)

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ