በአተት የተጠቁ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ነው
Ethiopia Zare (ሐሙስ ነሐሴ 21 ቀን 2001 ዓ.ም. August 27, 2009)፦ በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች በአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት ወይም በምህፃረ ቃል “አተት” ተብሎ በሚጠራው በሽታ የተጠቂዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ነው።
ሙሉውን አስነብበኝ ...Ethiopia Zare (ሐሙስ ነሐሴ 21 ቀን 2001 ዓ.ም. August 27, 2009)፦ በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች በአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት ወይም በምህፃረ ቃል “አተት” ተብሎ በሚጠራው በሽታ የተጠቂዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ነው።
ሙሉውን አስነብበኝ ...ፍርድ ቤቱ የአቶ ጌቱ ወርቁን የቪዲዮ ማስረጃ አልቀበልም አለ
Ethiopia Zare (ማክሰኞ ነሐሴ 19 ቀን 2001 ዓ.ም. August 25, 2009)፦ ከግንቦት ሰባት ንቅናቄ ጋር በተያያዘ ከተከሰሱት ግለሰቦች ውስጥ የንቅናቄው መስራች የሆኑት የአቶ አንዳርጋቸው አባት፣ አቶ ጽጌ ኃብተማርያምን ጨምሮ ሦስት ተከሳሾች ዛሬ የመከላከያ ምስክሮቻቸውንና የሰነድ ማስረጃዎቻቸውን ለፍርድ ቤቱ አቀረቡ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...Ethiopia Zare (ማክሰኞ ነሐሴ 19 ቀን 2001 ዓ.ም. August 25, 2009)፦ የመንግሥት የደህንነት ሰዎች፣ ካድሬዎችና የወረዳ ቀበሌ ሹማምንቶች፤ በአባላትና በደጋፊዎቻቸው ላይ ያልተቋረጠ የማወዋከብ ድርጊት እየፈጸሙ መሆኑን የኦሮሞ ፌደራሊስት ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ኦፌዲን) አስታወቀ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...Ethiopia Zare (ማክሰኞ ነሐሴ 19 ቀን 2001 ዓ.ም. August 25, 2009)፦ የደምወዝ ታክስ የሚቆረጥባቸው የመንግሥት ሠራተኞች፤ በአዲስ መልክ የተጀመረው የታክስ መክፈያ ማረጋገጫ የጣት አሻራ መስጠት ጉዳይ የደህንነት ሥጋት እየፈጠረባቸው መሆኑን ለኢትዮጵያ ዛሬ ገለጹ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...ገፍታሪዋ የወርቅ ሜዳሊያውን ተነጠቀች

Ethiopia Zare (እሁድ ነሐሴ 17 ቀን 2001 ዓ.ም. August 23, 2009)፦ በሴቶች 1500 ሜትር ርቀት ውድድሩን እስከ 1200 ሜትር ስትመራ የነበረችው አትሌት ገለቴ ቡርቃ በስፔይኗ አትሌት ናታሊያ ሮድሪከዝ ተገፍትራ መሬት ላይ በመውደቅዋ ውድድሩን ሳታሸንፍ ቀርታለች። ናታሊያ ውድድሩን በአንደኝነት ብትጨርስም ዳኖቹ አሸናፊነትዋን ውድቅ በማድረግ የወርቅ ሜዳሊያውን እንዳታገኝ አድርገዋል። ሙሉውን አስነብበኝ ...
በዓለም ሻምፒዮና በ10000 እና በ5 ሺህ በማሸነፍ ለዓለም የመጀመሪያው አትሌት ሆነ
(ተጨማሪ ፎቶግራፎች የታከለበት)

Ethiopia Zare (እሁድ ነሐሴ 17 ቀን 2001 ዓ.ም. August 23, 2009)፦ ኮከቡ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በበርሊኑ 12ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ5000 ሜትር አንደኛ በመውጣት ለራሱም ለሀገሩም ሁለተኛውን የወርቅ ሜዳሊያ አግኝቷል። በሻምፒዮናው በአስር ሺህ እና በአምስት ሺህ ወርቅ በማግኘት በዓለም ቀዳሚው አትሌት ሆኗል። ሙሉውን አስነብበኝ ...

Ethiopia Zare (እሁድ ነሐሴ 17 ቀን 2001 ዓ.ም. August 23, 2009)፦ ዛሬ እሁድ ነሐሴ 17 ቀን 2001 ዓ.ም. በጀርመን ዋና ከተማ በርሊን በተደረገው የሴቶች ማራቶን ከተሳተፉት አምስት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ውስጥ አሰለፈች መርጊያ ሦስተኛ በመውጣት ለኢትዮጵያ 4ኛውን የነኀስ ሜዳሊያ አስገኝታለች። ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኬንያውያን አትሌቶች ኢትዮጵያውያኑን በልጠው ተገኝተዋል

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ነሐሴ 16 ቀን 2001 ዓ.ም. August 22, 2009)፦ በዛሬው ዕለት (ቅዳሜ ነሐሴ 16) ስምንተኛ ቀኑን በያዘው በበርሊኑ 12ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በወንዶች ማራቶን 3ኛ፣ 4ኛ እና 15ኛ ሲወጡ፣ በሴቶች 5000 ሜትር ደግሞ 3ኛ፣ 4ኛ እና 5ኛ ወጥተዋል። የዛሬውን ሁለት የነኀስ ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ ያስገኙት አትሌት ፀጋዬ ከበደ በማራቶን፣ አትሌት መሰረት ደፋር ደግሞ በ5000 ሜትር ነው። ሙሉውን አስነብበኝ ...
‘ሌላው በአንድ ዓመቱ ታስሮ እየወጣ ልጄን አታስጨንቁት’ ወላጅ እናቱ
Ethiopia Zare (ቅዳሜ ነሐሴ 16 ቀን 2001 ዓ.ም. August 22, 2009)፦ የህወሓት መስራችና በአሁኑ ሰዓት ኢትዮጵያ ውሰጥ ያለው አገዛዝ አውራ ናቸው የሚባሉት የአቦይ ስብሃት ነጋ የ13 ዓመት ታዳጊ ወጣት ልጅ ነሐሴ 10 ቀን 2001 ዓ.ም. ከምሽቱ 4 ሰዓት ላይ አዲስ አበባ ውስጥ ሁለት ሰዎችን በመኪና ገጭቷል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...Ethiopia Zare (ዓርብ ነሐሴ 15 ቀን 2001 ዓ.ም. August 21, 2009)፦ በኢትዮጵያ የእስልምና ዕምነት ተከታዮች የረመዳንን ፆም ዛሬ ዓርብ ነሐሴ 15 ቀን 2001 ዓ.ም. ጀምረዋል። የአውሮፓ ሙስሊሞችም እንዲሁ በዛሬ ዕለት ፆሙን የሚጀምሩ ሲሆን፣ የሰሜን አሜሪካ ሙስሊሞች ደግሞ ነገ ቅዳሜ ነሐሴ 16 ቀን እንደሚጀምሩ ታውቋል። ሙሉውን አስነብበኝ ...