ቀነኒሳ በቀለ በበርሊን ሁለተኛውን ወርቅ ለማግኘት ማጣሪያውን አለፈ

Kenenisa Bekele, Berlin Aug 20, 2009ኢትዮጵያ በሜዳሊያ 8ኛ፣ በነጥብ 6ኛ ላይ ትገኛለች

Ethiopia Zare (ዓርብ ነሐሴ 15 ቀን 2001 ዓ.ም. August 21, 2009)፦ በጀርመን ዋና ከተማ በርሊን እየተካሄደ ባለው 12ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ባለፈው ሰኞ ነሐሴ 11 ቀን 2001 ዓ.ም. ኮከቡ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በአሥር ሺህ ሜትር ለኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳሊያ ካስገኘ በኋላ፤ በ5 ሺህ ሜትር ትናንት ሐሙስ ነሐሴ 14 ቀን በተደረገው የማጣሪያ ውድድር በ13፡19፡77 ደቂቃ በአንደኝነት ውድድሩን አጠናቅቋል። ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንድነት የጠራው የናዝሬቱ ስብሰባ በኦህዲድ ሰዎች ተበጠበጠ

Ethiopia Zare (ሐሙስ ነሐሴ 14 ቀን 2001 ዓ.ም. August 20, 2009)፦ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሰኞ ዕለት ነሐሴ 11 ቀን 2001 ዓ.ም. በሰጠው መግለጫ ላይ እንዳለው የናዝሬቱ ህዝባዊ ስብሰባ የተበጠበጠው “የክልሉ ቋንቋ፣ ወግና ባህል ባለመከበሩ” ሳይሆን የተደራጁና ሆን ብለው ረብሻ የመፍጠር ዓላማ ባላቸው በኦህዲድ የተደራጁ ኃይሎች ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ መንግሥት 10.5 ሚሊዮን ዶላር ካሣ ተፈረደለት

Ethiopia Zare (ሐሙስ ነሐሴ 14 ቀን 2001 ዓ.ም. August 20, 2009)፦ ሁለት ዓመት ለፈጀውና 80 ሺህ የሚሆን የሰው ልጆችን ሕይወት ለቀሰፈው ጦርነት መንስዔ የሆነውን ችግር ለመቅረፍና የሁለቱን ሀገሮች “ጦሰኛ” መንግሥታት ለመገላገል ችሎት የተቀመጠው የሔጉ ካሣ ኮሚሽን ለኢትዮጵያ መንግሥት 10.5 ሚሊዮን ዶላር ካሣ ይገባዋል! ይህንንም ኤርትራ ትክፈል ሲል ነሐሴ 11 ቀን 2001 ዓ.ም. ፍርድ ሰጥቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በምዕራብ ሸዋ ገበሬው ለማዳበሪያ ግዢ የእርሻ በሬዎችን ለመሸጥ ተገደደ

Ethiopia Zare (ሐሙስ ነሐሴ 14 ቀን 2001 ዓ.ም. August 20, 2009)፦ በምዕራብ ሸዋ አንቦ አቅራቢያ በሚገኘው ዳንዲ ወረዳ የሚገኙ ገበሬዎች ከአዝመራው ጊዜ ቀደም ብሎ ማዳበሪያ ባለማግኘታቸው በሬዎቻቸውን ለመሸጥ መገደዳቸውን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ጠቆሙ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዘመናዊው የጐጃም አዲስ አበባ መንገድ ጎሃ ጽዮን ላይ ተደረመሰ

Ethiopia Zare (ሐሙስ ነሐሴ 14 ቀን 2001 ዓ.ም. August 20, 2009)፦ በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የተመረቀውና “የሚሊኒየሙ ድልድይ” ወደ ተባለው የዓባይ ወንዝ መሸጋገሪያ የሚወስደው “ዘመናዊ” መንገድ ጎሃ ጽዮን ላይ በመደርመሱ መንገድ ተዘግቶ ግንኙነት ተቋርጦ እንደነበር ተዘገበ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የትራንስፖርት አገልግሎት መ/ቤት ከታክሲ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች ጋር እየተወያየ ነው

ሾፌሮችና ተራ አስከባሪዎች አደጋ ላይ ናቸው

Ethiopia Zare (ሰኞ ነሐሴ 11 ቀን 2001 ዓ.ም. August 17, 2009)፦ በዋና ከተማ አዲስ አበባ ነዋሪውን ህዝብ እየገጠመው ያለውን ችግር ለማስወገድ በሚል የትራንስፖርትና መገናኛ መ/ቤት ከታክሲ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች ጋር ውይይት ማካሄዱን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቴዲ አፍሮ ከእስር ከተለቀቀ በኋላ ያሉት ሁለት ቀናት በፎቶ

Talking with 2 mobiles, after one hour of his release እቤቱ ከገባ ከአንድ ሰዓት በኋላ በሁለት ሞባይል ስልክ ሲያወራ

Teddy Afro hugging his mother ቴዲ ልክ እቤቱ ሲገባና ከእናቱ ጋር ሲተቃቀፍ Ethiopia Zare (እሁድ ነሐሴ 10 ቀን 2001 ዓ.ም. August 16, 2009)፦ ባለፈው ሐሙስ ምሽት ላይ ዝነኛው ወጣት ድምፃዊ አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ከ484 ቀናት እስራት በኋላ ከእስር ነፃ ሆኗል። ከእስር ከተለቀቀ በኋላ ሐሙስ ዕለት ማምሻውንና የዓርብ ዕለቱን ሁኔታ በፎቶግራፍ ምን ይመስል እንደነበር እንደሚከተለው አቀናብረን አቅርበንላችኋል። ሙሉውን አስነብበኝ ...

በመጨረሻ ነፃ ሆነ - Free at last

Teddy Afro ቴዲ አፍሮ- እኔም ከቴዲዬ ጋራ አብሬ ተፈትቻለሁ - የቴዲ እናት

- መልካም ዕድል ይግጠምህ! - ዳኛ ልዑል ገ/ማርያም

- አመክሮው በ2 ዓመት ገደብ ተሰጥቶታል

- አድናቂዎቹ ደስታቸውን ገለፁ

ጽዮን ግርማ

የልደታው የፌደራል ከፍተኛና የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ግቢ ውስጥ መደበኛ ፍርድ ቤቶች የሚዘጉበት ወቅት በመሆኑ ፀጥታ ነግሷል። በከፍተኛው ፍርድ ቤት አሥራ ስድስት የወንጀልና አሥር የፍትሐብሔር መደበኛ ችሎቶች ሲኖሩ፤ ከሦስቱ መደበኛ የወንጀልና ተረኛ ችሎቶች በስተቀር የሁሉም ብረት በሮች ክርችም ተደርገው ተዘግተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መኢአድ በአፋር መንግሥት ተብጠለጠለ

‘የተቃወመው የአፋር ህዝብ አይደለም’ ኢንጂኒየር ኃይሉ ሻውል

Ethiopia Zare (ዓርብ ነሐሴ 7 ቀን 2001 ዓ.ም. August 14, 2009)፦ መኢኣድ ባለፈው እሁድ በዳግማዊ ምኒልክ ባደረገው ህዝባዊ ስብሰባ የተወካዮች ምክር ቤት ያፀደቀውን የሠንደቅ ዓላማ ዓርማ ለመጀመሪያ ጊዜ በአደባባይ የተቃወመ ሲሆን፣ የአፋር ክልላዊ መንግሥት ዓርማውን መቃወም የብሔረሰቦችን መብት መቃወም ነው ሲል መግለጫ አውጥቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ስዊድን ውስጥ ኢትዮጵያዊት ስደተኛ ተገደለች

Melete Kahssay, 25 ወ/ት ምልዕተ ካህሳይ ገዳይዋ ለፖሊስ እጁን ሰጠ

Ethiopia Zare (ሐሙስ ነሐሴ 7 ቀን 2001 ዓ.ም. August 13, 2009)፦ በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም በስደት ትኖር የነበረችና ወ/ት ምልዕተ ካህሳይ የተባለች የ25 ዓመት ወጣት ኢትዮጵያዊት ባለፈው ሣምንት ረቡዕ ዕለት የተገደለች ሲሆን፤ ገዳይዋም በማግስቱ እጁን ለፖሊስ መስጠቱን የኢትዮጵያ ዛሬ ሪፖርተር ዘገበ። 

ሙሉውን አስነብበኝ ...