ኢህአዴግ የትጥቅ ትግል የመረጡ ኃይሎችን የሚያጠናክር እርምጃ እየወሰደ መሆኑን መድረክ ገለጸ

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ኅዳር 13 ቀን 2001 ዓ.ም. November 22, 2008)፦ በኢትዮጵያ የመድብለ ፓርቲ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለመገንባት ፓርቲዎች ተደራጅተው ትግላቸውን የቀጠሉ ቢሆንም፤ ኢህአዴግ የፖለቲካ ምህዳሩን ከመቼውም ጊዜ የበለጠ እያጠበበ፣ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ጠንክረውና ደርጅተው እንዳይወጡ የሚያደርግባቸው ጫና እየከፋ ይገኛል በማለት መድረክ ለዲሞክራሲ ምክክር በኢትዮጵያ አስታወቀ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቅንጅት የበጀት ድጎማ እንዲለቀቅ ጠየቀ

Ethiopia Zare (ዓርብ ኅዳር 12 ቀን 2001 ዓ.ም. November 21, 2008)፦ መንግሥት በፓርላማ መቀመጫ ላላቸው ፓርቲዎች እሰጣለሁ ያለውን የበጀት ድጎማ አለመልቀቁ፣ የፓርቲዎችን የትግል እንቅስቃሴ ለማዳከም የተጠቀመበት ዘዴ መሆኑን የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ገለጸ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፊፋ የመጨረሻ ውሳኔውን አሳወቀ

‘ባለሀብቶች ተሰብስበው ፌደሬሽን ነን በማለታቸው ውሳኔያችን አይቀየርም’ ፊፋ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ኅዳር 9 ቀን 2001 ዓ.ም. November 18, 2008)፦ ዛሬ ማክሰኞ ጠዋት ሁለቱንም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ለማነጋገር በዙሪክ የተሰበሰበው ዓለማቀፉ የእግር ኳስ ፌደሬሽን (ፊፋ) ውሳኔው እንደማይቀየር አሳወቀ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንድነት ፓርቲ በስዊድን ከህዝብ ጋር ያደረገው ውይይት

የውይይቱን ክፍል አንድ በድምፅ ይዘናል (የማጫወቻው ችግር የተስተካከለ)

UDJ public meeting, Sweden

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ኅዳር 6 ቀን 2001 ዓ.ም. November 15, 2008) የአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ የአውሮፓ ልዑካን ቡድን የሆኑት የፓርቲው ሊቀመንበር ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ እና የፓርቲው የሥራ አስፈፃሚ አባልና የዕቅድና የስትራቴጂ ኃላፊ የሆኑት አቶ አክሉ ግርግሬ በስዊድን ዋና ከተማ ዛሬ ቅዳሜ ኅዳር 6 ቀን 2001 ዓ.ም. ከኢትዮጵያውያን ጋር ሲወያዩ ዋሉ። የእራት ግብዣም ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሹም ሽር በኦሮሚያ ክልል

የአዲስ አባባ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ የክልሉ ም/ፕሬዝዳንት ሆኑ

ም/ፕሬዝዳንቱ ወደ ኢህአዲግ ጽ/ቤት ተዛወሩ

አቶ በረከት ስምዖን ወደ ፈረሰው ማስታወቂያ ሚኒስቴር ሊመደቡ ይችላሉ

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ኅዳር 6 ቀን 2001 ዓ.ም. November 15, 2008)፦ ኀሙስ ዕለት የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት (ጨፌ ኦሮሚያ) ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ ሹም ሽር ማካሄዱ ታወቀ። ምክር ቤቱ ባደረገው ሹም ሽር የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብዱላዚዝ መሐመድን የኦሮሚያ ክልል ም/ፕሬዝደንት አድርጎ ሾመ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢቲቪ 32 ጋዜጠኞች ንብረት አስረክቡ ተባሉ

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ኅዳር 6 ቀን 2001 ዓ.ም. November 15, 2008)፦ የኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የቴሌቪዥን ዘርፍ፣ አዲስ በጀመረው የሰዓት ጭማሪና በጣቢያው ስር ይተዳደሩ የነበሩ የኦሮምኛና የትግርኛ ፕሮግራሞች ወደ ክልሎቻቸው እንዲሄዱ በተወሰነው መሰረት 32 የሚሆኑ የኦሮምኛ ፕሮግራም ሠራተኞች ንብረት አስረክባችሁ ክሊራንስ አስፈርሙ መባላቸውን ገለጹ። ክሊራንሱ ላይ ”በገዛ ፍቃዴ ለቅቄያለሁ የሚል ስላለው አንፈርም ብለናል” ሲሉ ሠራተኞቹ ገልጸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...