ያ’ገሬና የኔ (አትክልት አሰፋ - ከቫንኩቨር)

 ያ’ገሬና የኔ

 

(አትክልት አሰፋ - ከቫንኩቨር)

 እናቴና አገሬ ሙግት ገጠሙና

ሚስቴና እናት አለም ተወዳደሩና

ልጄ እና እማምዬ ፉክክር ገቡና

    አንዱን ምረጥ ብለው ድርቅ ሲሉብኝ፤

               እናቴም ውዴ ናት፣

               ሚስቴም የኔ ፍቅር፤

  ልጄም ንጉሴ ነው፤

                 የሚጣፍጥ ከማር

የግሌ የራሴ የማ’ለውጣቸው፣

በሰላሳ ዲናር የማልቀይራቸው፤

እናት፣ ሚስት፣ ልጄ፤ ሁሉም የኔ ናቸው።

             እኔ ግን ያገሬ፤

             እኔስ የ ‘ማምዬ…

የግል ንብረት ነኝ ብዬ መለስኳቸው።

 ዲሴምበር 15/2013- ቫንኩቨር (በርናቢ)

አገርና እንጀራ (ደመቀ ከበደ-ዓባይ ዳር) [ሊነበብ የሚገባ ምርጥ ቅኔ!])

አገርና እንጀራ / መቶ ሲደመር አንድ/
/ደመቀ ከበደ - ዓባይ ዳር/

ይቺ አገር - የኛ አገር
አንዴ ´ምትቦካ - አንዴ ´ምትጋገር፤
ሲሻ ´ምትወድቅ - ሲሻ ´ምትሻገር
አንዴ ባንተ ነበር - አንዴም በኛ ነበር፤

አገር እንደ ተረት - ‹‹ተረት›› ከተባለ
ተረት ነው አገርህ - በል ተርት ምናለ፤
አገር እንቆቅልሽ - ይሁን ከተባለ
‹‹እንቆቅልሽ አገር›› - ይኸውልህ አለ፤
አገር እንደ ፈሊጥ - ምሳሌ ከሆነ
ከኛዋ አገር በላይ - ምንም ‹‹ፈሊጥ›› የለ፤

አንዱ ‹ሲተርታት› - እሳት ዳር ቁጭ ብሎ
አንዱ ይሰማዋል - ‹‹የመሰረት›› ብሎ፤
ሌላው ‹እንቆቅልሽ› - ሲያደርጋት ጨክኖ
‹ምን አውቅልህ?› ይላል - ያኛው ከጎን ሁኖ፤
ቀሪው እንደ ‹ፈሊጥ› - ቃል ሲያሳምርባት
ይኸ በምሳሌው - አለ ሲስቅባት፡፡

ይቺ አገር - የኔ አገር
ይቺ አገር - የአንተ አገር
ይቺ አገር - የአንቺ አገር
ይቺ አገር - የኛ አገር / የሁላችን አገር /
አንዴ ስትቦካ - አንዴ ስትጋገር፤
በአቡኪና ጋጋሪ - ልኳ እየተለካ
ቀድሞ ባልተፈጨ - ሊጧ እየተቦካ
አለች እስከዛሬ - ሳትመር ሳትጥም
መጋገሪያው ምጣድ - ከሙግዱ ሳይገጥም፡፡

ለዚያም ነው
የዚያኛውን አቡኪ - ይኸ እየጋገረው
ያ የጋገረውን - አንዱ እየሰበረው
በሰባራ ምጣድ - እንደ እንኩሮ እንጀራ
በመጣ፤ በሄደ - አገሬ ተጋግራ
ይህንን እንጀራ
የመጣ ጋጋሪ - ወይም ባለተራ
ለባለ አገር ሁላ - ቢያበላ፣ ቢያበላ
ጠኔ አላጠገገም - ራብም አልከላ!

ምክንያት፤
የአያቶቹን ምጣድ - አባት እየሰበረ
የአባቶቹን ምጣድ - ልጅ እየቀየረ
አገር እያቦካ - ቀዬ እየጋገረ
እልፍኝ እያበጀ - ከልካይ እያኖረ
አብሲቱን ህዝብ ግን - ይረሳው ነበረ፤

እና እንዲህ እላለሁ፤
ማነህ ባለተራ?
ምጣድ ያዘጋጀህ - ለእንጀራ ጋገራ?!
እሳት ዳር ቁጭ ብሎ - ፍሙን እየሞቀ
ከትላንት ጥጥ ላይ - የታሪክ ባዘቶ - እየፈለቀቀ
እያጠነጠነ - ሸማ እያጠለቀ
ህዝብ ይኑርልኝ ካልክ - እየፈነደቀ
በሰባራ ምጣድ - ሊጥ አታነካካ
ባለፈው ጋጋሪም - ሙያህን አትለካ
ይልቅ የእልፍኙን ሰው - ሌማቱ እንዲያረካ
በአገር ልክ ጋግር - ከህዝብ ጋር አቡካ!!
Photo: አገርና እንጀራ / መቶ ሲደመር አንድ///ደመቀ ከበደ - ዓባይ ዳር//ይቺ አገር - የኛ አገርአንዴ ´ምትቦካ - አንዴ ´ምትጋገር፤ሲሻ ´ምትወድቅ - ሲሻ ´ምትሻገርአንዴ ባንተ ነበር - አንዴም በኛ ነበር፤አገር እንደ ተረት - ‹‹ተረት›› ከተባለተረት ነው አገርህ - በል ተርት ምናለ፤አገር እንቆቅልሽ - ይሁን ከተባለ‹‹እንቆቅልሽ አገር›› - ይኸውልህ አለ፤አገር እንደ ፈሊጥ - ምሳሌ ከሆነከኛዋ አገር በላይ - ምንም ‹‹ፈሊጥ›› የለ፤አንዱ ‹ሲተርታት› - እሳት ዳር ቁጭ ብሎአንዱ ይሰማዋል - ‹‹የመሰረት›› ብሎ፤ሌላው ‹እንቆቅልሽ› - ሲያደርጋት ጨክኖ ‹ምን አውቅልህ?› ይላል - ያኛው ከጎን ሁኖ፤ቀሪው እንደ ‹ፈሊጥ› - ቃል ሲያሳምርባትይኸ በምሳሌው - አለ ሲስቅባት፡፡ይቺ አገር - የኔ አገርይቺ አገር - የአንተ አገርይቺ አገር - የአንቺ አገርይቺ አገር - የኛ አገር / የሁላችን አገር /አንዴ ስትቦካ - አንዴ ስትጋገር፤በአቡኪና ጋጋሪ - ልኳ እየተለካቀድሞ ባልተፈጨ - ሊጧ እየተቦካአለች እስከዛሬ - ሳትመር ሳትጥምመጋገሪያው ምጣድ - ከሙግዱ ሳይገጥም፡፡ለዚያም ነውየዚያኛውን አቡኪ - ይኸ እየጋገረውያ የጋገረውን - አንዱ እየሰበረውበሰባራ ምጣድ - እንደ እንኩሮ እንጀራበመጣ፤ በሄደ - አገሬ ተጋግራይህንን እንጀራየመጣ ጋጋሪ - ወይም ባለተራለባለ አገር ሁላ - ቢያበላ፣ ቢያበላጠኔ አላጠገገም - ራብም አልከላ!ምክንያት፤የአያቶቹን ምጣድ - አባት እየሰበረየአባቶቹን ምጣድ - ልጅ እየቀየረአገር እያቦካ - ቀዬ እየጋገረእልፍኝ እያበጀ - ከልካይ እያኖረአብሲቱን ህዝብ ግን - ይረሳው ነበረ፤እና እንዲህ እላለሁ፤ማነህ ባለተራ?ምጣድ ያዘጋጀህ - ለእንጀራ ጋገራ?!እሳት ዳር ቁጭ ብሎ - ፍሙን እየሞቀከትላንት ጥጥ ላይ - የታሪክ ባዘቶ - እየፈለቀቀእያጠነጠነ - ሸማ እያጠለቀህዝብ ይኑርልኝ ካልክ - እየፈነደቀበሰባራ ምጣድ - ሊጥ አታነካካባለፈው ጋጋሪም - ሙያህን አትለካይልቅ የእልፍኙን ሰው - ሌማቱ እንዲያረካበአገር ልክ ጋግር - ከህዝብ ጋር አቡካ!!

ዋ ማዲባ ዋ ማንዴላ (ዘምንሊክ)

ዘምንሊክ ከሲድኒ
ኔልሰን ማንዴላ Nelson Mandela
ዋ ማንዴላ!
ዋ ማዲባ!
ይቺን ፀሐይ ማን ነገረህ
ከጨለማ ውስጥ በቅለህ
ከድጥ ወደ ማጥ ብትዳክር
ብርሃን በልብህ አሳድረህ
"እንካቹ!" ብትል ብትጮህ
ሰሚ ተነፍጎህ
አንድ ቀን እንደሚነጋ
በደልና ግፍ ማክተሚያ እንዳለው ስትዘክር፤

ለተጨቆነ እንዲበራ

ቃል ተጋብተህ እስክትሞት እንደምትዳክር።
ንገረኝ ማዲባ
ጥርኽልኝ ማንዴላ
ማን ነገረህ እንዲህ እንዲነጋ?
ግዙፉን ያፓርታይድ ዱላ
ሳትሰለች ቅንጣት ሳትፈራ

ቢወርድብህ

በወጣት ዘመን ቢቸክህ፤

እግርህ በግረሙቅ ታብቶ

እኩል ዕድሜህን ቀምቶ

በግዞት ቢጠበጥብህ
የልብህ ብርሃን በራ እንጅ
መች ተረታህ ለፈረንጅ።
ይቺን ቀን ፀሐይ እንድትፈካ ለጭቁኖቹ
እንድትበራ ማን ሹክ ብሎህ ይሆን ምስራቹን?
ዋ ማዲባ!
ዋ ማንዴላ!
የሰባዊነት ትሩጁማኑን ባንታየን


ቢተቹህ ቢንቁህ
ሰላማዊ ትግልህን ቢያንጓጉጡህ
የልብህን ብርሃን መች አወቁ?

ትግልህ አፋፍ ላይ ደርሶ

ሰላም ለህዝብህ አንግሶ

ሥልጣን በጅህ ሲገባ

ያቺን የልጅነትህን ብርሃን

በመካያው ላለም ብታሰፍን፤
ጥቁር የሰላም ፀር ይመስል
ዓለም በራድ ቆዝሞ -

በደም መቃባት በበቀል
ዛሬ- ነገ ፈነዳ ብሎ -

በሰቅቀን ተብሰክስኮ
ጉድ ለማየት ሲያደባ
ተቃቅፈህ ጸናህ ከዴክለርክ፤
ሰላም መስፈኑን አበሰርክ።

ዋ ማንዴላ!

ዋ ማዲባ!

እንዴት ይሆን

የገባህ ፍቅር

እንዴት ይሆን

የገባህ መላ

ዋ /ን/ ማን ማንዴላ!!!
እነንቶኔ
አንሰው አንሰው
ከዘር ወርደው
ብሔር ከጎሣ ሰፍረው
ሰፍረው
ቁ-ል-ቁ-ል
ደ-ቅ-ቀ-ው
ተ-በ-ጣ-ጥ-ሰ-ው
በሥልጡን ዘመን
ፊት ገ-ጥ-ጠ-ው
ገዢ ነን ብለው
ካገር ከህዝብ ተስፈንጥረው
እንደማይጸግብ መጋዣ -
የህዝቤን ደም መ-ጥ-ጠ-ው፡
መ'ጠው፡
አሳፈሩን በመሪ ስም ስናያቸው፡
ማይችሉት መንበር ላይ ሲንቧቸሩ ብናያቸው።

አንተ ግና

የበቀል ፍሬ እንዳይረባ

ባስደናቂ ፍቅር አስተጋባህ፤
ዋ ማንዴላ! ዋ ማዲባ!
የሰላም የፍቅር ሐውልት
የጥቁር ብልህ ተምሳሌት ።
----------//-------------
ዘምንሊክ
ከሲድኒ፣ ዲሴምበር 6፣ 2013 እ.ኤ.አ.

አፍሪካዊው ኮከብ (አበራ ለማ)

አበራ ለማ
ኒልሰን ማንዴላ Nelson Mandela

ጀግናው አሸለበ፣ ደከመው ተረታ

ሞት አይቀርምና፣ የማታ የማታ፤

ምን ብርቱ ቢሆኑ፣ ሺ መካች ቢሆኑ

ሰው አያልፍ አይገደፍ፣ ተዛቹ ተቀኑ፤

አፍሪካ ሆይ መጥኔ፣ አንድ ወልደሽ ላጣሽው

ተንግዴ መሸብሽ፣ በማን ትዘክሪው? በማንስ ትጠሪው?

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ