ሣሙኤል ይሄነው This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

አብዛኛው ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያዊ የሚስማማበት ጉዳይ ቢኖር የችግሮቻችን መጠን፣ አይነቶችና ምንጮቻቸው ቢለያይም ቅሉ፤ ችግሩ ግን በዘር፣ በቀለም፣ በጎሣ፣ በጾታ፣ በዕድሜ፣ … ወዘተ ሳይለይ የእያንዳንዱን ቤት በየተራ ማንኳኳቱ ነው። ኑሮ የከበደው፤ ነፃነቱን ተገፍፎና ተረግጦ ያለው፤ የተራበው፤ ፍትህ የተጠማው፤ … እከሌ ተከሌ ሳይባል አብዛኛው ኢትዮጵያዊ እንደሆነ ይታወቃል። ይሄ እውነት ከሆነ ታዲያ ለውጥ ማምጣት እንዴት ከበደን? የምር የተገፋና የመረረው ህዝብ እንዴት ዝም ይላል?

 

ምክንያቱ ደግመን ድጋግመን የሰማነው፤ ነገር ግን በደንብ አላምጠን ውጠን ከዚያም ደግሞ መተግበር የተሳነን ጉዳይ ነው - ተባብሮ በአንድነት መታገል አለመቻል! ሰፊው ህዝብ በአንድነት መታገል ካልቻለ ደግሞ በተናጠል ጉዞ የአንዳችንንም ችግር መፍታት እንደማንችል በንድፈ ሃሳብ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በ97 ምርጫ ጊዜም በተግባር ግልጽ የሆነ ጉዳይ ነው። ወይ ተባብሮ መዳን ነው፤ ካልሆነ ተሰባብሮ ማለቅ ነው - (We stand together or perish alone!)። (ሙሉውን ጽሑፍ በፒ.ዲ.ኤፍ. አስነብበኝ!)

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ