”ጴጥሮስ ያቺን” ቃል (መክብብ ማሞ)

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

Abune Petros አቡነ ጴጥሮስ መክብብ ማሞ ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. )

”ፋሺስቶች ያገራችንን አርበኞች ሽፍታ ቢሉዋቸው እውነት እንዳይመስላችሁ። ሽፍታ ማለት ያለ ሀገሩ መጥቶ የሰውን ሀገር የሚወር ይህ በመካከላችሁ መጥቶ የቆመ አረመኔው የኢጣሊያ ፋሺስት ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ለእርሱ እንዳይገዛ ውጉዝ ነው። የኢትዮጵያ መሬት እንዳትቀበለው የተገዘተች ትሁን!” አቡነ ጴጥሮስ።

ያለፈው ረቡዕ ሐምሌ 22 ቀን ጀግናው ሰማዕት አቡነ ጴጥሮስ በግፍ የተገደሉበት 73ኛ ዓመት ነበር። እኒህ ታላቅ አባት ለሰማዕትነት ያበቃቸው ዋናው ምክንያት በወቅቱ ለተጠየቁት ቀላል ለሚመስል ጥያቄ፤ ”ቃሌን አልክድም” ብለው በመቆማቸው ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“የኢትዮጵያና ኤርትራ ፌዴሬሽን አስፈላጊነት” ፕ/ር ዳንኤል ክንዴ

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

Administrative Mapበካሊፎርኒያ ሳን ዮሴ ባለፈው ግንቦት 7 ቀን 2001 ዓ.ም. በተካሄደው የኢትዮጵያውያንና የኤርትራውያን የወዳጅነት ኮንፈረንስ ላይ ፕ/ር ተስፋጽዮን መድኅኔ እና ፕ/ር ዳንኤል ክንዴ ተናጋሪዎች እንደነበሩ መዘገባችን አይዘነጋም። “የኢትዮጵያንና የኤርትራን ወንድማማች ህዝቦች ሊቀራርብ የሚችለው የኮንፌዴሬሽን ሥርዓት ነው” በማለት ፕ/ር ተስፋጽዮን መድኅኔ ”ኢትዮጵያና ኤርትራ ከየት ወዴት?” በሚል ርዕስ ባቀረቡትን ጽሑፍ አስነብበን የፕ/ር ዳንኤል ክንዴን ጽሑፍ ለማቅረብ ቃል ገብተን ነበር። ፕ/ር ዳንኤል ክንዴ “የኢትዮጵያና ኤርትራ ፌዴሬሽን አስፈላጊነት” በሚል ርዕስ ያቀረቡትን ጽሑፍ ታነቡ ዘንድ እንጋብዛለን። መልካም ንባብ!

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የደሴ ህዝብ - ተረኛው የመስዋዕትነት ጠቦት? (መሣፍንት)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

መሣፍንት ዘፈረንሣይ ለጋሲዮን (አዲስ አበባ) ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. ) ሐምሌ 2001 ዓ.ም.

ከሣምንታት በፊት ያደመጥኩት አንድ ዜና በርካታ ነገሮችን ወደ አዕምሮዬ እያመላለሰና ከዚህ በፊት ተሰምቶኝ የማያውቅ ስሜት በውስጤ እየፈጠረ ፋታ ሲነሳኝ ይህችን ወረቀት ጫጭሬ የተሰማኝን ለወገኖቼ ባካፍልስ ብዬ አሰብኩና ብዕሬን አነሳሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያውያን ስፖርት ፌስቲቫል 2009 ግምገማ (ክንፉ አሰፋ)

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

ክንፉ አሰፋ 3 August 2009

Pairs Ethio-Festival 2009"... ከሁለቱ የመጫወቻ ሜዳዎች ትይዩ ባለች አንድ ዛፍ ጥላ ስር በርጫና ሽሻው ሞቅ ብሏል። ለየት ባለ መልኩ “ለመዝናናት የመጡ” ወጣቶች ሕይወታቸውን ይቀጫሉ። ጫትን በግልጽ መቃምም ሆነ መሸጥ አይከለከልም። “ኢትዮጵያም አይከለከልም” ያለኝ ወዳጄን አልረሳውም። “ይህ የኢትዮጵያን ባህልም የምናንጸባርቅበት መድረክ ነው። ሀገራችን ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጀምሮ ሁሉም በግልጽ ነው የሚቅመው።” ነበር ያለው። እውነቱን'ኮ ነው። ለኳስ ከመጣው ለጫት የመጣው ይበልጥ ነበር። በዚሁ ከቀጠለ በቅርብ ጊዜ የስፖርቱ ፌዴሬሽን - የአውሮፓ የጫትና ሺሻ ፌዴሬሽን የማይሆንበት ምንም ምክንያት አይኖርም። ..." በማለት በፓሪስ የተካሄደውን በአውሮፓ የኢትዮጵያውያን የስፖርትና የባህል ፌስቲቫልን የገመገመው ጋዜጠኛ ክንፉ አሰፋ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለሱማሌ መፍትሔ የአራትዮሽ ውይይት መጀመር ያስፈልጋል

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

ዳኮታ የጥናት ማዕከል

(አልሽባብ፤ ኢትዮጵያዊ ኃይል፤ የኤርትራና የአሜሪካ መንግሥት)

ሱማሌ የአልሽባብ ተዋጊዎች 98%፤ እነመለስና አሜሪካኖች ሊያቆሙት የሚፈልጉት መንግሥት ሁለት በመቶውን የሱማሌ ግዛት ተቆጣጥሮ ነው ያለው። መንግሥት ተብዬው እራሱን ከአልሽባብ ታጋዮች ከመከላከል በስተቀር ለማጥቃትና ይዞታውን ለማስፋፋት ምንም አቅም የለውም። እስከጭራሹም ሱማሌን ለቆ እንዲወጣ ቀነ ቀጠሮ እየተቆረጠለት ነው ያለው። የበዙት የህዝብ ተወካዮች፤ የመንግሥቱ ባለሥልጣናት ወደተለያየ ሀገር ጥለው ፈርጥጠዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ብሔራዊ ተጠያቂነት ያልከበደው የአንድነት አታካራ (ስሜነህ)

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

“… የእኛን መለያየት ልዩ የሚያደርገው በሃሳብ ከእኛ የተለየን የራሳችንን ወገን ከምድረ ገጽ ድራሹን ካላጠፋንና ሞራሉን አንኮታኩተን እርኩሳዊ እርካታን ካላገኘን እንቅልፍ ያለመተኛታችን አባዜ ነው። ወይ እኛ አንተኛ ወይ ሰው አናስተኛ። ግራ የገባን፣ ቀናነት የጎደለን፣ … ህዝቦች። የተለያዩ ልምዶችም ሆኑ የ2 ሺህ ዓመት ሚሊኒየም ምንም ያላስተማሩን። …” የሚሉት በስዊድን የቀድሞ ቅንጅት በኋላም የአንድነት የድጋፍ ሰጪ ማኅበር ዋና ፀሐፊ የነበሩት አቶ ስሜነህ ታምራት ናቸው። አቶ ስሜነህ በተለይ ለኢትዮጵያ ዛሬ የሰጡትን ጠንከር ያለ አስተያየት ታነቡ ዘንድ እንጋብዛለን። መልካም ንባብ!

ሙሉውን አስነብበኝ ...