”ጴጥሮስ ያቺን” ቃል (መክብብ ማሞ)
መክብብ ማሞ ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. )
”ፋሺስቶች ያገራችንን አርበኞች ሽፍታ ቢሉዋቸው እውነት እንዳይመስላችሁ። ሽፍታ ማለት ያለ ሀገሩ መጥቶ የሰውን ሀገር የሚወር ይህ በመካከላችሁ መጥቶ የቆመ አረመኔው የኢጣሊያ ፋሺስት ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ለእርሱ እንዳይገዛ ውጉዝ ነው። የኢትዮጵያ መሬት እንዳትቀበለው የተገዘተች ትሁን!” አቡነ ጴጥሮስ።
ያለፈው ረቡዕ ሐምሌ 22 ቀን ጀግናው ሰማዕት አቡነ ጴጥሮስ በግፍ የተገደሉበት 73ኛ ዓመት ነበር። እኒህ ታላቅ አባት ለሰማዕትነት ያበቃቸው ዋናው ምክንያት በወቅቱ ለተጠየቁት ቀላል ለሚመስል ጥያቄ፤ ”ቃሌን አልክድም” ብለው በመቆማቸው ነበር።
ሙሉውን አስነብበኝ ...


"... ከሁለቱ የመጫወቻ ሜዳዎች ትይዩ ባለች አንድ ዛፍ ጥላ ስር በርጫና ሽሻው ሞቅ ብሏል። ለየት ባለ መልኩ “ለመዝናናት የመጡ” ወጣቶች ሕይወታቸውን ይቀጫሉ። ጫትን በግልጽ መቃምም ሆነ መሸጥ አይከለከልም። “ኢትዮጵያም አይከለከልም” ያለኝ ወዳጄን አልረሳውም። “ይህ የኢትዮጵያን ባህልም የምናንጸባርቅበት መድረክ ነው። ሀገራችን ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጀምሮ ሁሉም በግልጽ ነው የሚቅመው።” ነበር ያለው። እውነቱን'ኮ ነው። ለኳስ ከመጣው ለጫት የመጣው ይበልጥ ነበር። በዚሁ ከቀጠለ በቅርብ ጊዜ የስፖርቱ ፌዴሬሽን - የአውሮፓ የጫትና ሺሻ ፌዴሬሽን የማይሆንበት ምንም ምክንያት አይኖርም። ..." በማለት በፓሪስ የተካሄደውን በአውሮፓ የኢትዮጵያውያን የስፖርትና የባህል ፌስቲቫልን የገመገመው ጋዜጠኛ ክንፉ አሰፋ ነው። 


