“እርካብና መንበር”ን አየኋት፤ ኢትዮጵያ እርምሽን አውጪ!

እርካብና መንበር

ገ/ክርስቶስ ዓባይ

“እርካብና መንበር” በ'ዲራአዝ' የብዕር ስም የተጻፈች እጥር ምጥን ያለች መጽሐፍ ናት። መጽሐፏ እጅግ በሠፊው የተወራላት በመሆኗ በእጄ እንደገባች በጥንቃቄ እና በጥሞና ማንበቤን ቀጠልሁ። ጸሐፊው ያላቸውን ራዕይና የሞራል ጥንካሬ በሚገባ አይቼበታለሁ። ከልብ በመነጨ ስሜትና ጉጉትም እንደተጻፈ ለመገንዘብ ችያለሁ። ምናልባት ጸሐፊው የአስተዳደርን ጥበብ ለማወቅ፤ አንድም በተወሰነ ርዕስ ላይ በአተኮረ ጥናት መጻሕፍትን ሲበረብሩ፤ አልያም ስለአመራር የተለያዩ ሥልጠናዎችን የመካፈል ዕድል ያጋጠማቸው እንደነበር መገመት አይከብድም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያዊነት፤ ሰው የመኾን ሕይወትን የሚያቀነቅነውን የ‘ምሥራቃዊት ኮከብ’ ፖለቲካዊ ልቦለድ ድርሰትን በጨረፍታ

ምሥራቃዊት ኮከብ
ኒቆዲሞስ

እንደ መንደርደሪያ

የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሀብት/የኢኮኖሚክስ ምሩቅ፣ የዓለም ሰላምና ዕርቅ ግብረ ሠናይ ድ/ት የሥራ ባልደረባና የኢኮኖሚክስ መምህር የሆነው ወጣቱ ጸጋዘአብ ለምለም ተስፋይ በ2010 ዓ.ም. ባሳተመውና በ336 ገጾች በተቀነበበው በ‹ምሥራቃዊት ኮከብ› ፖለቲካዊ ድርሰት ላይ በጥቂቱ የግሌ ምልከታና አስተያየት የተካተተበት የወፍ በረር ዳሰሳ ለማድረግ ወደድኹ። በቅድሚያ ግን በመጽሐፉ የፊት ሽፋን ገጽ ላይ በተካተቱት ሥዕላት ላይ ጥቂት ሐሳቦችን በማንሳት ልንደርደር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ስውሩና ያልታወቀው ታሪክ”

The Hidden and Untold History of the Jewish People and Ethiopians by Fikre Tolossa

የመጽሐፍ ርዕስ፦ ስውሩና ያልተነገረው የአይሁዳውያን እና የኢትዮጵያውያን ታሪክ

ደራሲ፦ ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ ጅግሳ

አሳታሚ፦ ንባዳን ኃ.የተ.የግል ማኅበር (Nebadan plc)

የገጽ ብዛት፦ 234 (ከአባሪዎችና ምስሎች ጋር)

ዳሰሳ አቅራቢ፦ ሚኪያስ ጥ.

ሰውዬው በትምህርቱና በሥነ-ጽሁፉ ዓለም ከከረሙ፣ ዘመን አልፏቸዋል። ኢትዮጵያ እያሉ ካሳተሟት፣ “ወለላ” ከተሰኘች የአጫጭር ልቦለዶች መድበል አንስቶ እስከዛሬ እስከጻፏቸው ታሪክ-ቀመስና ልቦለዳዊ ሥራዎቻቸው ድረስ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅናን አትርፈዋል። በአሁኑ ሰዓት በዩኒቨርሲቲ ኦፍ ሊንኮልን (university of Lincoln) በመምህርነት እየሠሩ ይገኛሉ፤ ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኅቡእ ጣት (ዘ ሀይድ)፣ አዲስ መጽሐፍ

ሸንቁጥ አየለ

ኅቡእ ጣት (ዘ ሀይድ)
ኅቡእ ጣት (ዘ ሀይድ)፣ የሸንቁጥ አየለ አዲስ መጽሐፍ

ኅቡእ ጣት (ዘ ሀይድ) የተሰኘውን አዲሱ መጽሐፌ፤ በኢትዮጵጵያውያን፣ ኤርትራውያን እና ግብጻውያን፤ ብሎም በተጓዳኝ ያሉ አገራትን ፖለቲካዊ ስነልቦናዊ ጭብጥ፣ የፖለቲካ ኢኮኖሚያዊ ስሌት፣ አገራዊ ራዕይ፤ እንዲሁም አጠቃላይ የፖለቲካ ቀመራዊ ውል ሊፈትሽ ይባትታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ድር ያደራበት ብዕርዎትን ከሰገባው ባያወጡት ይሻል ነበር!”

“... መሃል ፒያሳ ላይ መርከብ እንዲያንሳፍፍልዎ ነበር እንዴ የፈለጉት? ወይስ አይሮፕላን አኮብኩቦ እንዲያሳርፍልዎ?”

መዝገቡ ሊበን ከሜነሶታ

Yetekolefebet qulf

አልታዬ የተባሉ ጸሃፊ በቅርቡ “... ለረጅም ዓመታተ የጣሉትን ብዕር ድር ካደራበት ሰገባው ...” መዝዘው “የተቆለፈበት ቁልፍ” በቃላት ቁልፍ ተቆላልፏል!” በሚል ርዕስ አስነብበውናል። ዶ/ር በፍቃዱ በቀለ በ“የተቆለፈበት ቁልፍ” መጽሐፍ ላይ በጻፉት ግምገማ ላይ ተነስተው ትችታቸውን ያስነበቡን አልታዬ፣ ከስነ-ጽሁፋዊ ትችታቸው በፊት ያስቀደሙት፣ ዶ/ር በፍቃዱ፣ በ‘የተቆለፈበት ቁልፍ’ መፅሐፍ ላይ ያቀረቡት ጽሁፍ“...የወዳጅነት ፍቅር፣ አክብሮትና ስሜታቸውን ነው ... ወይስ በእውነት ምክንያታዊ ትችታቸውን?!...” በሚል፣ ምናልባትም “speculation” (ተጨባጭ ማስረጃ የሌለው “ቲዎሪ”) ነው። እንኳንስ አይደለም “ወዳጅ”፤ አባት እና ልጅ ቢሆኑስ አልታዬን ምን አገባዎት? ልጅ የአባቱን፣ አባት የልጁን ስነ-ጽሁፍ ስራ ቢተች ምን ችግር አለው? ትኩረትዎን ለምን ሃሳቡ እና ጽሁፉ ላይ አላደረጉም? ወዳጅነታቸውንስ መጥቀስ ለምን አስፈለገ? “speculation” ካልሆነ ደግሞ የዶ/ር በቀለን እና የደራሲውን ወዳጅነት አልታዬ ያውቃሉ? ምናልባትም ጽሁፉ ከእውነተኛ ስነ-ጽሁፋዊ ትችት ይልቅ “character assassination”/ሃሳብን ሳይሆን ግለሰብን ማጥቃት (ad hominem) አያስመስልብዎትም?

ሙሉውን አስነብበኝ ...

"የተቆለፈበት ቁልፍ" በቃላት ቁልፍ ተቆላልፏል

አልታዬ ገብረመድህን

Yetekolefebet qulf

ለረጀም ዓመታተ የጣልኩትን ብዕር ድር ካደራበት ሰገባው እንድመዝ አስገደደኝ - (Ethiomedia) ድረ-ገፅ ላይ ከወራት በፊት በዶክተር ፍቃዱ በቀለ በተባሉ ግለሰብ በ"የተቆለፈበት ቁልፍ" መጽሐፉ ላይ የቀረበ አንድ ፅሑፍ።

"ሃያሲው" በዘመናችን አቻ ያላገኙለት (ወደር የሌለው) መጽሐፉ መሆኑን ነው የገለፁልን።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለተከበሩ ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ

ሰላ አቦምሳ

የኦሮሞ እና የአማራ እውነተኛው የዘር ምንጭ + ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ

ለተከበሩ ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ፣ ለጤናዎት እንደምነዎት። በእርሶና በፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ መሃል ያለውን የሃሳብ ልውውጥ ከተመለከትኩ በኋላ የግሌን አስተያየት ለመስጠት ወሰንኩኝ። የሃሳብ ልውውጡን እንደተመለከትኩኝ ከሆነ መሪራስ አማን በላይ አንዱ የክርከሩ አካል እንደሆኑ ተረዳሁ። በዚህም መሰረት ስለ መሪራስ አማን በላይ ለማወቅና እሳቸውን በአካል ለማግኘት ካልሆነም ያሳተሟቸውን ለማግኘት ሞከርኩ። በአካል ማግኘት ባይሳካልኝም ፤ 10 የሚሆኑ ያሳተሟቸውን መጻሕፍት አገኘሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሳባ ንግሥት ትሩፋትና የዶክተር ጌታቸው ኃይሌ ስህተት

Prof. Getatchew Haileሙሉጌታ ውዱ

መግቢያ፤

ዶክተር ዶናልድ ሊቫይን የሚባል በቺካጎ ዩኒቨርሲቲ አስተማሪ የሆነ አንድ "አይሁድ" አሜሪካዊ የዛሬ አሥራ ስድስት አመት አካባቢ እኔ ወደምኖርበት አካባቢ መጥቶ ደወለልኝና በቀጠሮ ተገናኝተን በአንድ የኢትዮጵያ ምግብ ቤት ውስጥ አብረን መመገብ ጀመርን። በጭውውታችን መካከል ስለ ኢትዮጵያውያን "ምሁራን" አነሳና አስተያየቱን ይሰጠኝ ጀመር። ከሁሉም የሚወደው (my favorite በሚል አገላለፅ) እንድርያስ እሸቴ የሚባለውን ሰው እንደሆነ ነገረኝ። አከታትሎም በእንግሊዝኛ አግቦ አነጋገር ኢትዮጵያዊ ሊቅ (በምዕራባዊ ትምህርት) እኮ የለም አለኝ። የተጠቀመው የእንግሊዝኛ ቃል "true scholar" የሚል ነበር። ያን ጊዜ ብዙ ኢትዮጵያውያን "ምሁራን" (በምዕራባዊ ትምህርት) አሉ ብየ የማስብበትና ደረቴን የምነፋበት ጊዜ ስለነበረና ገና ብዙ ያልመረመረ የጎልማሳነት ስሜት ሰለነበረኝ በሰውየው አነጋገር ስሜቴ ተጎዳ። እኔም ጥድፊያ ከሚበዛባቸው ሥራዎቼ ፋታ ሳገኝ የኢትዮጵያን ጉዳይ እና ታሪኳንም ማጥናት ጀመርኩ።የዶክተር ዶናልድ ሊቫይንን ሥራዎችም በቅርብ ማየት ጀመርኩ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ ከፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ (ክፍል ሁለት)

ፍቅሬ ቶሎሳ ጂግሳ (ፕ/ር)

Merriras Aman Belay Certofocate

ውድ ፕሮፌስር ጌታቸው ኃይሌ

"ለውድ ፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ፣ የውውይቱ መንስኤ" በሚል ርእስ ባለፈው ሳምንት ያቀረቡአቸውን የትዕቢት ናዳዎችን፣ የብስጭት ውርጅብኞችንና የመከላከያ እሩምታዎችን ንቄ ትቼ፣ በእርስዎ ደረጃ ዝቅ ላለማለት ስል ከነሱ ውስጥ መልስ መስጠት ያለብኝን ብቻ በመጀመሪያ እሰጥና ወደ ቀድሞ ጥያቄዎቾ እመለሳለሁ። መልሶቼ ሁሉ ተደምረው የሌሎቹንም ግለሰቦች ሁሉ ጥያቄዎች ይመልሳሉ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ። በጥንቃቄና በቀና ልብ ያነበቡት ሰዎች ሁሉ መጽሐፉ ራሱ ጥያቄዎቻቸውን መልሶላቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለፕ/ር ጌታቸው ኃይሌና ለፕ/ር ጳውሎስ ሚልኪያስ መልስ

Prof. Getachew and Fikres bookየኢትዮጵያ ታሪክ ጽሁፍ ገና ተጀመረ እንጂ አላለቀም

ስሜ ላቀች አክሊሉ ይባላል፣ እዚህ አሜሪካ አገር ከመምጣቴ በፌት በፈረንሳይ አገር ፓሪስ ጥቂት ዓመታት ኖሬአለሁ፤ እኔ የታሪክ ጸሃፊም ተመራማሪም አይደለሁም። ብዙ ግዜም በሚድያ ለሚወጡ ጹሑፎችም መልስ አልጽፍም።

ነገር ግን የኢትዮጵያን ታሪክ ጥናት ከሚያካሂዱ ሰዎች ዘንድ(ነፍሳቸውን ይማርና ከእነ ፕሮፌሰር ዮሴፍ ቱቢያና)ለተወሰነ ጊዜ ተሳትፌአለሁ። የአገሬም ታሪክ እግዚአብሔር ኢትዮጵያዊት አድርጎ እስከፈጠረኝ ድረስ በሰፊው ይመለከተኛል ብየ አስባለሁ። አሁን ይህን ሰሞን በፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ መጽሐፍ ላይ የተነሳውን ስድብና ውዝግብ ማየቴ በግድ ካለሁበት እንድወጣ አድርጎኛል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ