ቅምሻ ጨዋታ “ሞተዋል እንዳልል ቀብርዎን አላየሁ፤ አሉም እንዳልልዎ ድምፅዎን አልሰማሁ …”

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ  PM Meles Zenawiአቤ ቶኪቻው

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ምን ውስጥ እንደገቡ እስከ አሁንም የጠራ ወሬ አልሰማንም። በምትኩ የተምታታ ዜና እያዳመጥን ነው። ቅዳሜ እለት ለህትመት የበቃው እንግሊዘኛው “ፎርቹን” ጋዜጣ መለስ ወደ አዲስ አበባ መመለሳቸውን አስመልክቶ ፊት ለፊት ገፁ ላይ አስነብበቦን ነበር። ዛሬ ደግሞ ሪፖርተር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ውጪ ሃገር በእረፍት ላይ ናቸው ብሎ ዘግቦልናል። ነገሩን ልብ ብለን ስናየው ዘጋቢዎቻችንም እየዘገቡልን ሳይሆን እያወዛገቡን ነው የሚመስለው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በራስ ላይ ችግር በመፍጠር እንደህወሓት ማንም የለም

ታረቀኝ ሙጬ

በራስ ላይ ችግር በመፍጠር እንደህወሓት ያለ ጅላንፎ የትም የለም - ለነርሱ እርግጥ ነው የብልጣብልጥነት መለያቸው መሆኑ ነው። ኢሕአዲግ የህወሓት የመሀል አገር ስም መሆኑን መቼም ማንም አያጣውም። ለዚህ ነው በርዕሴም ሆነ በዚህ አንቀጽ መጀመሪያ ይህን የማጭበርበሪያ ካባ ላነሳ ያልወደድኩት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

”ያበደች ሴት …“

ዮሐንስ በቀለ ከጀርመን

የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል በዓመት ሁለት ጊዜ ይከበራል። በሰኔና በህዳር ወር። በዚሁ መሰረት የ2004 ዓ.ም. የሰኔ ሚካኤል በዓል ሰኔ 10 ቀን 2004 ዓ.ም. በጀርመን ኮሎኝ ከተማ በሚገኘው በደበረሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ተከብሯል። ይህ ቤተክርስቲያን በሃገሪቱ የመጀመሪያውና ባሁኑም ጊዜ የራሱን ቤተክርስቲያን ገዝቶየሚገለገል ብቸኛው ቤተክርስቲያን ነው። በርካታ ሌሎች ቤተክርስቲያናትንም አፍርቷል። የተመሰረተበትን ሰላሳኛ ዓመት በሚቀጥለው የፈረንጆቹ 2013 ያከብራል፤ ዝግጅቱ ካሁኑ እየታሰበበት ነው። ሃሳቤ ስለቤተክርስቲያኑ ታሪክ ለማውራት ስላልሆነ፤ ከዚህ በላይ አልቆይበትም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

”ፅንስም ከሆነ ይገፋል ...”

ይኸነው አንተሁነኝ

የጎጠኛው መለስ ዜናዊን ሰሞንኛ ሁኔታ አስመልክቶ የሚባሉ፣ የሚተረኩና የሚጻፉ የተለያዩ አመለካከቶችንም ሆነ መላምቶችን ጨምሮ የደጋፊና የተቃዋሚ ምኞቶችን ያካተቱ መረጃዎች ይወጣሉ። መረጃዎች አንደኛው ከሌላኛው የመደጋገፋቸውን ያህል በዚያው ልክ ፈጽሞ የተራራቁ፣ የማይዛመዱና ከዚያም ሲያልፍ በፊት የተጻፉትን የሚቃወሙና የሚተቹ ቁጥራቸው ጥቂት ባለመሆኑ፤ የሆነውን ትክክለኛ ነገር ለማወቅ ለሚፈልገው የኢትዮጵያ ህዝብና አንባቢ ግራ አጋቢ ሁኔታን ፈጥሯል። ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ? ...

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ… (የግል አስተያየት - በአያልሰው ደሴ)

’በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ’፣ በዙሪያ ጥምጥም ችግሮች ላይ ”የሕገ-መንግሥት” ቀውስ ሲታከል

የዜጎችን አንድነትና እንደ-ሕዝብ በጋራ መቆምን የግድ የሚል ዳግም የፈተና ጊዜ

አያል ሰው ደሴ (የግል አስተያየት) ሐምሌ ፲ ቀን ፪ ሺህ ፬ ዓ.ም.

(ከሁሉ በፊት የዚህ አጭር ጽሑፍ ዓላማ መነሻው የአቶ መለስ ዜናዊን የጤንነት ሁኔታ የተመረኮዘ ይሁን እንጂ ስለጤንነታቸው ይዞታም ሆነ እሳቸው ላይ ያተኮረ እንዳልሆነ ይታወቅልኝ።) የህወሓቱ የዕድሜ-ልክ መሪና ላለፉት ሃያ-አንድ ዓመታት በኢትዮጵያ አገራዊ ሥልጣን ቁንጮ ሆነው የቆዩት አቶ መለስ ዜናዊ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ለሕይወታቸው ያሰጋ ከፍተኛ የጤና መታወክ የደረሰባቸው የመሆኑ ዜና ከተሰማ ጀምሮ የኅብረተሰባችን ዋነኛ የመወያያ ርዕስ እንደሆነ ይታወቃል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመለስ መንፈስ

ክንፉ አሰፋ

የሞዛምቢኩ መሪ የነበሩት ጀነራል ሳሞራ ማሼል በአውሮፕላን አደጋ በ1986 (እ.ኤ.አ) በሞቱ ጊዜ ወዳጃቸው ኮ/ል መንግስቱ በአደባባይ ወጥተው፤ "ሳሞራ አልሞተም! ሳሞራ በመካከላችን አለ!" ብለው ሲናገሩ ትዝ ይለኛል። አለም አቀፍ ሜዲያው የሚለው ሌላ - እሳቸው የሚነግሩን ሌላ። ነገሩ በለጋነት አስተሳሰብ ግራ ያጋባል። ኮሎኔሉ የሚናገሩት እንዳሁኑ ጥሬ ውሸት ሳይሆን፤ የሳሞራን በመንፈስ አለመለየት መሆኑ ቆይቶ ነበር የገባኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለውጥና ማምከኛ የወያኔ ስልት

ዳዊት ዋስይሁን

ለውጥ የተፈጥሮ ህግ ነው። ነገሮች በህዋችን ውስጥ በማያቋርጥ አንቅስቃሴ እና ለውጥ ላይ እንዳሉ ሳይንሱ አረጋግጦታል። አገራችን እና ሕዝቦችዋ ለውጥን ከተራቡና ከናፈቁ አመታት ተቆጠሩ። ከዚህ በፊት ህዝቡ ተስፋ ጥሎባቸው ከፍተኛ መስዋእትነት ከፍሎባቸው የነበሩ የለውጥ ወቅቶች በኛ እንዝላልነትና በገዢዎቻችን ብልጣብልጥነት ከእጃችን ላይ በቀላሉ ሲነጠቁ አስተውለናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ፤ ከሥዩመ-እግዚአብሔር ወደ ሥዩመ-ፓርቲ

ሰሎሞን ተሠማ ጂ. (semnaworeq.blogspot.com)

የፖለቲካ ጭንቀቱና ጥበቱ ስለውክልና ጉዳይ ነው። የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ባላቸው አስተሳሰብና አመለካከት መሰረት በፖለቲካው ሸንጎ/መድረክ መወከል አለባቸው። ብዙኃንም ሆኑ ጥቂቶች ውክልና ሊኖራቸው የተገባ። አለበለዚያ፣ “አልተወከልኩም” የሚል የህብረተሰብ ክፍል ወደ አመጽና ነውጠኝነት ያዘነብላል። ያ ደግሞ ለማንም፣ በምንም መልኩ ፋይዳ-ቢስ ነው። በተለይም ያልሰለጠነና በድህነት አረንረቋና ውስጥ የሚኖር ህዝብ ከሆነ የሚከተለው መዘዝ ቤተ-መንግስትን ብቻ ሳይሆን ሃገርንም ያወድማል። ሶማሊያ ጥሩ ምሳሌ ናት። አልተወከልንም የሚሉ ጎሳዎች የጫሩት እሳት መላ ሃገሪቱንና አካባቢውን መለብለብ ከጀመረ እነሆ ሃያ አራት አመት ደፈነ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መለስ “የአፍሪካ ተወካይ” የት ገቡ?

ግርማ ደገፋ ገዳ This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

በ2006 (እኤአ) የኩባው ፊደል ካስትሮ “ሞቱ!” ሲባል፣ በማያሚ (ፍሎሪዳ) መንገዶች ላይ ዳንስና ጭፈራ ነበር የተከተለው። የመኪና ጡሩምባ፣ ጩኸት፣ ፉጨት፣ የላቲን ሙዚቃና ውዝዋዜዎች በአናት በአናቱ ሲንቆርቆሩ ነበር ሌሊቱ የነጋው። ፊደል ካስትሮ ፕሬዚዳንት ስለመሆናቸው ሳይሆን፣ ኩባዊ ሰው ስለመሆናቸው ብቻ እያሰቡ እንኳ ያዘኑ የሉም። ወደ ኢትዮጵያ ዞር ስንል፣ የኢሕአዴጉን ጠቅላይ ሚኒስትር አስመልክቶ፣ አንዳንድ ሚዲያ ላይ ያልወጡ የሚያስቁም የማያስቁም ወሬዎች አሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ምንም ላለመተካት መተካካት (አስራደው ከፈረንሣይ)

አሥራደው (ከፈረንሣይ)

ሰሞኑን የአቶ መለስ ዜናዊ መታመም ጉዳይ በአገር ውስጥና፤ ከአገር ውጪ ባሉት የሥርአቱ ደጋፊዎች ዘንድ፤ እንዲሁም የአቶ መለስ የጡት አባቶች በሆኑት ምዕራባዊ አገራት፤ በአፍሪካ የዕድሜ ልክ ሥሌጣን ባለቤቶች፤ የኢትዮጵያ መሬት በርካሽ በተቸበቸበላቸው የአረብ አገራትና፤ በተጨማሪም የአገራችን በር ወለል ተደርጎ ተከፍቶላቸው እንደልባቸው በሚምነሸነሹት ቻይናና ሕንድች ሳይቀር፤ የስጋት አውሎ ንፋስ አንፍሷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ