የጠቅላይ ሚኒስትሩ የልማት ሠራዊት የሀገሪቱን አንጡራ ሀብት ሲያባክን

ኢንጂነር አብደልወሃብ ቡሽራ - መGለ

በትግራይ ክልል የልማት ሠራዊት እንዲሆኑ ተብለው የተመደቡ አካላት የወረዳና የቀበሌ አስተዳዳሪዎች በሕወሓት ካድሬ መሪነት ነው እሚንቀሳቀሱት። የታዘዙትን የሚፈጽሙ ናቸው። እነዚህ አካላት የተሰማሩበት የሥራ ዓላማ በገጠር በተመረጡ ቦታዎች በመስኖ የሚለማ ግብርና ማፋጠን የሚል ነው። ለዚህ ተብሎ የታቀደው የልማት አቅጣጫ ደግሞ በተመረጡ የገጠር መንደሮች እያንዳንዱን ገበሬ በእርሻ ማሣው የውሃ ጉድጓድ መቆፈር እንዳለበት ነው። በተጨማሪ ከደደቢት የብድር ተቋም የውሃ ሞተር በብድር መልክ በመውሰድ ከጉድጓድ ውሃ እየመጠጠ ወደ እርሻ ማሳ እንዲጠያሰራጭ ታስቦ ነው። ለዚህ ጉዳይ የተመደበው ባጀት እንደሚከተለው ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኤፍሬም ማዴቦ የረሳት ሞገደኛዋ ሚስት

ነጻነት ዘገዬ

ባልና ሚስት ነበሩ። ሚስት ጣም እልኸኛ ናት። ባልዬው ታጋሽ ነው። እርሱዋ ሁል ጊዜ ተቃራኒ ናት። ባልዬው እንብላ ሲላት እስዋ እንሂድ ትላለች፤ እንሂድ ሲላት እንቀመጥ ትላለች፤ በዚህ መልክ እየተዳረቁ ይኖራሉ - ኑሮ ካሉት መቃብርም እንደመሞቁ። በአንድ አጋጣሚ አሳድሩኝ ባይ አንድ የወንድ እንግዳ ወደቤታቸው ይመጣል። ይሄኔ የሚስቱን ጠባይ የዘነጋ ባል ምን ይላል፤ ‹እኔና እንግዶ መደቡ ላይ እንተኛለን፤ አንቺ ከልጆችሽ ጋር እግገኑ ላይ (የገጠር ቤት ሣሎን ማለት ነው) አንጥፋችሁ ተኙ›። ሚስት ሆይት ባል ተናግሮ ሳይጨርስ ካፉ ቀለብ ታደርግና ‹ እንዴት ተደርጎ? ሞኝህን ፈልግ! አንተና ልጆችህ እግገኑ ላይ እኔና እንግዶ እመደቡ ላይ ነው እምንተኛ› ትልና ዘራፍ ትላለች። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሁለተኛ ግፌ ጫንቃዬን ተገርፌ ልብሴን መገፈፌ

ዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል

በሀገሬ ሳለሁ፥ ለዓመታት ከለፋሁበት የትምህርት ገበታዬ ተፈናቅዬ፣ ያለፍርድ ቤት ማዘዣ ወረቀት ተይዜ ከአንዴም ሁለቴ ለእስር የተዳረግኩ፣ በሞትና በህይወት መካከል የተገረፍኩና የተደበደብኩ፣ በመጨረሻም ሀገሬን ለቅቄ በባዕድ ምድር ያለ አንዳች ረዳትና የህይወት ዋስትና በእንግድነት እንድኖር የተገደድኩ ስዘርፍ፣ ሳምጽና የሰው ሚስት ሳማግጥ ተገኝቼ ወይም ተደርሶብኝ ሳይሆን ሕገ መንግስታዊ (አንቀጽ 29) መብቴን በመጠቀም ጸረ-ቤተ ክርስቲያን፣ ጸረ ሀገርና ጸረ ትውልድ በሆነው ድብቅ አጀንዳ ያለው ማህበር ላይ “ማህበረ ቅዱሳን ወይስ ማህበረ ሰይጣን?” በማለት በበርካታ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሕጋዊ ሰነዶችና ደብዳቤዎች የተደገፈ ከጻፍኩት መጽሐፍ የተነሳ ነበር። የታሪኩ አንዳኛ ምዕራፍ መሆኑ ነው! ሙሉውን አስነብበኝ ...

”ተቃወሙት” ስለተባለው አዲስ ቤተክርስቲያን

በስዊድን “አዲስ ቤተክርስቲያን ይከፈታል" መባሉን ምዕመናን ተቃወሙት በሚል ለቀረበ ጽሑፍ የተሰጠ ምላሽ

ቀሲስ ፍሰሐ ተስፋዬ

መግቢያ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! አለመታደል ሆነና ዛሬ አውላላ ሜዳ ላይ ቆሜ የማስነብባችሁ ነገር ከላይ በጠቀስኩት ብሎግ ላይ ስማችንን ለማጉደፍ የፈለጉ አንድ ግለሰብ በእኔ፣ በአቡነ ኤልያስና በአባ ኒቆዲሞስ ላይ የጻፉትን የሐሰት ውንጀላ ለማስተባበልና እውነቱን ለማሳየት ነው። ራሴን አስተዋውቄ ዝርዝር ነገሩን በመጠኑ አስረዳለሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ልዩ ቅኝ ግዛት

ይነጋል በላቸው

አንድ በወያኔው መንግሥት መሥሪያ ቤት የሚሠራ ባልንጀራ አለኝ። ባለፈው ሰሞን ድንገት ተገናኘንና ሻይ ቢጤ ይዘን ስለዚችው መከረኛ ሀገር ስንጫወት ብዙ ነገር ገረብን። ዛሬ ጊዜ መገረብ ካልሆነ አዲስ ነገር መቼም አልተገኘም። በሀገርና በብዙኃኑ ዜጎች የሚወርደው የሥቃይና የመከራ ዶፍ እንደሆነ በዓይነቱና በይዘቱ እየሰፋ ከመሄድ በስተቀር ሲቀንስ አልታየም፤ እናም እሱም አዲስ ሳይሆን ያው የለመድነው ነውና እንደለመድነው ለ‹ሪከርድ› ያህል አሁንም ጥቂት እንገርብ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመንግሥት ሌቦች አደራ-ቢስነትና ሕዝብ ኃላፊነት

ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተደጋጋሚ ስለመንግሥት ሌቦች እየተናገረ ነው፤ ሌቦቹን ግን እሱም አያውቃቸው፤ እነሱም እየሰሙት አይደለም፤ የመንግስት ሌቦች የተባሉት የሚግጡባቸው ዋናዎቹ መስኮች ታክስ፣ መሬትና የንግድ ውድድር መሆናቸውንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጾአል፤ ከዚህም በላይ የተባሉትን የሌብነት መስኮች ከለምነት ወደበረሃነት ለመለወጥ የኢትዮጵያ ህዝብ ኃላፊነት አለበት ያለ መሰለኝ፤ ሥልጣን ሳይኖር ኃላፊነት ከየት ይመጣል? ሙሉውን አስነብበኝ ...

አገር በምን ይፈርሳል?

ተመስገን ደሳለኝ

በእርግጥም ይህ ወቅት በዚህ ጉዳይ ላይ እንድንነጋገር የምንገደድበት ነው። ጉዳዩ የግራ-ዘመሞች ወይም የቀኝ መንገደኞች ፖለቲካ አይደለም። ጉዳዩ ኢህአዴግን የመጥላት ወይም የመውደድ አይደለም። ጉዳዩ መለስ ስልጣናቸውን ይለቃሉ ወይስ አይለቁም የሚል አይደለም። ጉዳዩ የገዥው ፓርቲ ወይም የተቃዋሚዎችም አይደለም … የሀገር ጉዳይ እንጂ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኤፍሬም እሸቴ: ብትስማማ ነው እንጂ የሚያስደምመው ባለመስማማትህ ምን ይደንቃል?

ዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል

ጥብቅ ማሳሰቢያ:- ጽሑፉ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር በመደገፍ የተጻፈ ጽሑፍ አይደለም። ጽሑፉ ኤፍሬም እሽቴ የተባለው አንድ "የማህበረ ቅዱሳን" የስራ አመራር አባል ግለሰብ “ጠ/ሚኒስትሩ ስለ ማኅበረ ቅዱሳን በተናገሩት አልስማማም” ሲል ከግንዛቤ እጥረት የተነሳ በጻፈው የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ያን አስተምህሮ የማይወክል ዝርው ይዘት ያለው ጥሬ ጽሑፍ አስቸኳይ እርምት እንዲደረግበትና በክርስትና ስም በአንባቢያን ላይ የፈጠረውን ብዥታ ግምት ውስጥ በማስገባት የተጣራ ምስል ለመስጠት ኩልል ቅልብጭ ባለ መልኩ የተዘጀ ጽሑፍ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ይድረስ ላስጠራዥ - መለስ ዜናዊ (ከተጠራዥ ስደተኛ)

ዳዊት አበበ Dawit Abebeከተገኘ ነውጠኛ ሊሆን ነው ቃተኛ!!

ይድረስ ላስጠራዥ - መለስ ዜናዊ

ከተጠራዥ ስደተኛ - ዳዊት አበበ / ኦስሎ ኖርዌይ

በሽተኛ - የማስታወስ ችሎታዬ ከጠፋ ሰነባብቷል፣ አንዳንድ ጊዜ በመንገድ ላይ ሆኘ ሳለሁ ከቤቴ ተነስቼ ወደ ቢሮዬ መሄዴን?፣ ወይ ደግሞ ከቢሮዬ ወጥቼ ወደ ቤቴ መመለሴን እስከማላውቅበት ድረስ ይምታታብኛል መድሃኒቱ ምንድነው ብሎ ይጠይቃል ዝንጉው- ህመምተኛ ሳይካትሪስቱን።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ