“ካርቱም ሄዶ ቀረ” እንዲሁም “ካምፓላ ሄዶ ተቀረቀረ”

ክፍሉ ሁሴን

ስደት ለወሬ ያመቻል እንዲሉ በ1999 ዓ.ም ስደት ከገባሁ ጀምሮ መጽሐፍ እጽፋለሁ እያልኩ እንደፎከርሁ አለሁ። ሳልሞክር ግን አልቀረሁም። በተለያየ ጊዜና በተደጋጋሚ እያነሳሁ ከጣልኩ በኋላ ለስንፍናዬ መጽናኛ ያደረኩት በቅርቡ እስተወዲያኛው ያሸለበው ስብሃት ገብረእግዚያብሄር በአንድ ወቅት በራዲዮ ቃለምልልስ “ከመጻፍ መኖር ይበልጣል፤ የምንጽፈው ከኑሮ ነውና” ያለውን በመውሰድ ‘መች ኖርኩና ለመጻፍ እጋበዛለሁ’ ብዬ ራሴን ቀስ በቀስ በቁመና እየገዘገዝኩት እገኛለሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የቅሌትና የውርደት ዘመን

ፍቅር ይበልጣል (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.)

እንዴት እንደከረማችሁ እያወቅሁት ‹እንዴት ከረማችሁ› ብዬ አልጠይቅም። ሲዳሩ ማልቀስ ወግ መሆኑ እዬቀረ እንደመምጣቱ ሁሉ ሲገናኙ ሰላምታ መለዋወጥም እንደዚያው እየሆነ ነው። ምን አዲስ ነገር አለና? ጊዜ ማጥፋት ብቻ! ሁሉም ነገር ያው ነው ብቻ ሳይሆን ያው መሆንም እያቃተው ከሴከንድ ወደ ሴከንድ እየባሰበት ነው የሚሄደው - በኢትዮጵያ ውስጥ የሚታየው ነባራዊ ሁኔታ በተለይ - በዓለም ዙሪያ ደግሞ ባጠቃላይ። ተግባባን?

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለምን ኢትዮጵያዊ ፍልስፍና …?

ካሳሁን ዓለሙ ወልዴ

‹የጥንታዊ ኢትዮጵያን ጥበብ› የሚዳስሱ መረጃዎችን ለመሰብሰብ ስውተረተር ‹Encarta 2009›ን ስለኢትዮጵያ ፍልስፍና ምን እንደያዘ ጠየቅኩት። የአውሮፓ ነው ያለውን ከጥንታዊት ግሪክ ጀምሮ እስከ ዘመናዊ አሜሪካ ድረስ ያሉ የፍልስፍና ዓይነቶችን ዘርዝሮ አቀረበልኝ፤ ወደ ህንድና ቻይናም ሔዶ አማረጠኝ፤ ወደ መካከለኛው የእስልምና ዓለም ፍልስፍናም ወስዶ አስጎበኘኝ። ሆኖም ምንም እሱ በዚህ መልክ ቢያማርጠኝም እኔ ‹ጥያቄዬ አልተመለሰም› አልኩት፤ ሐቀኛው Encarta እንኳን በኢትዮጵያ በአጠቃላይ በአፍሪካ ፍልስፍና መኖሩን እንዳማያውቅ እቅጩን አረዳኝ። ይህም የቀድሞው የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት የነበሩት ዶክተር አክሊሉ ሀብቴ የተናገሩትን አስታወሰኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የደራሲና ጋዜጠኛ ማሞ ውድነህ የህይወት ታሪክ ዳሰሳ

ደራሲና ጋዜጠኛ ማሞ ውድነህ Author & journalist Mamo Wudnehበወሎ ክፍለ ሃገር፣ የዛሬ 81 ዓመት የተወለዱት ማሞ ውድነህ፣ ወላጆቻቸውን በአምስቱ አመት የጣሊያን ወረራ ጊዜ ነው ያጡት። ማሞ ውድነህ 12ኛ ክፍልን ያጠናቀቁት ገና በ15 ዓመት እድሜያቸው መሆኑ በጊዜው ተደናቂ ወጣት አድርጓቸው ነበር። ከዚያም ወደ ጽሁፍ ዓለም በመዝለቅ እጅግ በርክታ መጻህፍትን ሲጽፉ፣ ብዙዎች፣ በተለይ በስለላ ሥራ ላይ ያተኮሩ መጻህፍትን ተርጉመዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መሪዎቻችን እነማን ናቸው? አርቲስቶቹ ወይስ ታጋዮቹ?

አቤ ቶኪቻው

ከላይ በርዕሱ እንደተገለፀው ለዛሬው የፍትህ ጋዜጣ ጨዋታችን በዋነኛነት ይዤ የመጣሁት ጉዳይ መሪዎቻችን እነማን እንደሆኑ የሚጠይቅ ነው። ያው እንደተለመደው ሌሎች ጨዋታዎችም ይኖሩናል። አውራ ርዕሱ ግን “መሪዎቻችን እነማን ናቸው… አርቲስቶቹ ወይስ ታጋዮቹ?” የሚለው ይሆናል። “ለፓርቲ አውራ እንዳለው ሁሉ ለጨዋታም አውራ አለው።” እንልና ገዢው ፓርቲን ገልመጥ እናደርጋለን…

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፈራ ይመለስ

ተመስገን ደሳለኝ

የፈራ ይመለስ። አዎ ይመለስ! ግን ከየት ነው የሚመለሰው? መችስ ወጣና ነው የሚመለሰው? እንዴት ነው ነገሩ ሁሉ እኮ፡-

መች ተዋጋና

ያስባል ገና


መሰለብንሳ። እውነት ግን በዛሬ ቀን ስለፍርሃት መወራት አለበት? ያውም በታላቁ የዐድዋ ድል ቀን፤ ለነገሩ ይሄ ድል ብቻ አይደለም-ከዐድዋ፤ የ‹‹ፍርሃት ኪኒን›› ፋርማሲስቱም ከዐድዋ ናቸው መሰለኝ፡፡ አይ ዐድዋ! ዋ አንቺ ዐድዋ…። ስለዐድዋ ብዙ ተበሎአል። ብዙም ተነግሮአል። ሆኖመ ከሁሉም ከሁሉም ለልብ የሚቀርበው ኢትዮጵያውያን አዝማሪዎች የገቡበትን የፍርሃት ጠርሙስ ፈንቅላ የወጣችው ጂኒ (ጂጂ)፣ ያች የጎበዝ ወዳጅ ‹‹ትናገር ዐድዋ›› ስትል በዛ በተስረቅራቂ ድምጿ ያቀነቀነችው ነው። አዎን! ትናገር ዐድዋ፡- ሙሉውን አስነብበኝ ...

የጅብ እርሻ የዶር. ዳኛቸው መዝገብ

ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማሪያም

የዶ/ር ዳኛቸው የጅብ እርሻ የኢትዮጵያን ሁኔታ በትክክል የሚገልጽ ጽሑፍ ነበር፤ ብዙ ሰዎች እንዳነበቡት ተስፋ አደርጋለሁ፤ ካላነበቡት ፈልገው ቢያነብቡት ማወቅ ለሚፈልጉ ሰዎች ይጠቅማል፤ ዳኛቸው ከመንገድ ላይ ያገኛትን የአነጋገር ፈሊጥ ለቁም-ነገር አበቃት፤ ጅብ በተፈጥሮ ባሕርዩ አያርስም፤ ፍሬም አይለቅምም፤ ድንገት ተሳስቶ ቢያርስም እስቲበቅል ለመጠበቅ ትእግስቱ የለውም፤ ዳኛቸውም የጅቡን እርሻ ‹‹በአንድ በኩል የኢሕአዴግን አካሄድ በሌላ በኩል በተቃዋሚ ፓርቲዎች መሀከል የሚካሄደውን ሁኔታ ሊያስረዳልኝ/ሊገልፅልኝ የሚችል…›› ነው በማለት ይጠቀምበታል። ሙሉውን አስነብበኝ ...

እነ ‘አሽከር’ ወለተ አማኔል በአደዋ ድል ይታወሱ!

አትክልት አሰፋ (ቫንኩቨር-ካናዳ)

ከ116 ዓመት በፊት በዚህች እለት ድል የሚባል ታላቅ ነገር በዚያች ኢትዮጵያ የምትባል የአለም ግምባር የነበረችና መልሶ ደግሞ ደብዛዋ በጠፋ ሀገር ላይ ተበሰረ። እናም ታላቅ ደስታ ከታላቅ የደም ጎርፍ በሗላ ሆነ። ከድንቅ የጦር ውሎ ለጥቆ፤ ያለ አቻ የተደረገ የግንባር ለግንባር ጦርነት ከተጠናቀቀና የነ አትንኩኝ ባይ ምድር ላይ የደም ጎርፍ ከተጥለቀለቀ በሗላ በኢትዮጵያ ምድር ነጻነት ይፋ ተደረገ። በአለም ዙሪያ ያሉ ጥቁር ህዝቦችም ሰው መሆናቸውን፤ ማሸነፍ ምን ማለት እንደሆነ አውቀው የነጻነትን ተስፋ ይሰንቁ ዘንድ አፍታም አልወሰደባቸውም። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአንዱዓለም አራጌና የሌሎችም የፖለቲካ እስረኞች ግፍና መከራ

ከፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረ ማርያም

ትርጉም ከነጻነት ለሃገሬ

በቀድሞው ሶቭየት ሕብረት ስርአት ውስጥ የሰብአዊ መበት ተሟጋቾችንና ተቃዋሚ ፕርቲዎችን እያጎረ በስቃይ ይጠብሳቸው የነበረበት የስርአቱ ገሃነም‹‹ጉላግ›› ወህኒ ቤት ነበር፡፡እነዚህ ‹‹ገሃነሞች›› ጉላጎች ተግባራቸው፤ በሶቭየት ሕብረት ያሉትን ተቃዋሚዎች በአጠቃላይ ለማጥፋትና ዳጋም እንዳያቆጠቁጡ ማደረግ ነበር፡፡የሶቭየት የሽብርና የመከራ ቁጥቋጦዎች ሆነው ያደጉና የሃገሪቱና የህዝቦቿ ቀንደኛ ጠላቶች ነበሩ፡፡በተላበሱት የጭካኔና ኢሰብአዊነት ጎሬነታቸው ‹‹የሥጋ መፍጪያዎች›› በሚል ይታወቁ ነበር፡፡ ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ