የሀብታሙ አያሌው ባለ አራት ምዕራፍ ፖለቲካ

ይገረም አለሙ

ሀብታሙ አያሌው
አቶ ሀብታሙ አያሌው

አቶ ሀብታሙ አያሌው እሱም ብዙ እያለ ስለ አርሱም እየተባለ ነው። ፖለቲካችንም ማህበራዊ ኑሮአችንም የተቃኘው በእውነት ላይ ሳይሆን በስሜት ላይ ሆነና አፍቅረን ሰንደግፍ ሆነ ጠልተን ስንነቅፍ ምክንያት ብቻ አይደለም ለከትም የለንም። ሜዳው ላይ ልጆች በዙና፣ ጨዋነት እየኮሰመነ ዋልጌነት እየገነነ መጣና ትላልቆቹ ዕድሜ ጠገቦቹ ተግባራቸው አገር ሊያድን፣ ረጋ ሰከን ብሎ ነገሮችን ግራ ቀኝ አይቶና መዝኖ የመደገፍም የመንቀፍም ባህል የሌለን መሆናችን ሰሞኑን በአቶ ሀብታሙ አያሌው ዙሪያም እየታየ ነው። ሜዳው ላይ ልጆች በዝተው ጨዋነት እየኮሰመነ ዋልጌነት በመግነኑ ትላልቆቹ ስራቸው አገር ሊያድን ምክራቸው ትውልድ ሊቀርጽ የሚችሉቱ አፋቸው ከመናገር እጃው ብእር ከማንሳት በመቆጠቡ ነገራችንን በደንባራ በቅሎ ቃጭል ተጨምሮ እንዲሉ አድርጎታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ይድረስ ለሚመለከታችሁ ባለሥልጣናት (የማለዳ ወግ)

ነቢዩ ሲራክ

* ለአንባሳደር አሚንና ለአንባሳደር ውብሸት ባላችሁበት

* ቅጅ፣ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባለሥልጣናት
አንባሳደር አሚን፣ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁና አንባሳደር ውብሸት

መረጃን ማቀበሌ ወንጀል ሆኖ "የነቢዩ ሲራክ ልጆች ከሚማሩበት የጅዳ ኮሚኒቲ ትምህርት ቤት እንዲታገዱ" የሚለው የካድሬዎች ሀሳብ ያን ሰሞን ቀርቦ እንደነበር በድጋሜ በማረጋገጤ አዝኘ ነበር ያደርኩት። ... ስለ እውነት ለመናገር፣ ስለ እውነት እየተገፉ መኖር ግድ ይላል ብዬ የሚሰራው ባይደንቀኝም በዘመነ ኦሪት እንኳ ባልታዬ ህግ ልጆች በአባታቸው "ወንጀል" ስማቸው ሲጠራ መስማት ልቤን በሀዘን ሰብሮት አድሯል። እናም ሁሉንም ለመርሳት ልጆቸን እረፍት ወደ ማይሰማ ወደ ማይናገረው ቀይ ባህር ይዣቸው ዘና ልበል ብዬ ማልጀ ስነሳ ሌላ አሳዛኝ መረጃ ደረሰኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሞረሽ፣ ዋናውን ነገር ገሸሽ

ይገረም አለሙ

Major Dawit Woldegiorgis
ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ

ሻ/ቃ ዳዊት ወልደ ጊዮርጊስ ሲያትል በአገራዊ ንቅናቄው ስብሰባ ላይ የተናገሩትን አዳመጥኩት፣ ከዚህ ንግግር በመነሳት ከተጻፉት አንዳዶቹንም አነበብሁ “የሻለቃ ዳዊት የዋሽንግተን ሲያትል ንግግር በሞረሽ ዕይታ!” የሚለው ጽሁፍ በሁለት ምክንያት ቀልቤን ሳበው። የመጀመሪያውና እንዳነበው የገፋፋኝ በድርጅት ስም የተጻፈ መሆኑ ሲሆን፤ ይህችን አስተያየት እንድጽፍ ያበቃኝ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ በሻ/ቃ ዳዊት የተነሱና ሞረሽ ከጻፈ አይቀር ምላሽ ሊሰጥባቸው ይገቡ የነበሩ አበይት ጉዳዩችን ወደ ጎን የተወ ሆኖ ማግኘቴ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መንግሥትነት ከቤት ይጀምራል

ምሕረት ዘገዬ

Charity
Charity begins at home

ፈረንጆች “Charity begins at home” ይላሉ። እንዲህ ሲሉ መልካምነት ወይም በጎነት ከቤት እንደሚጀምር ለመግለጽ ነው። እኔም ከዚህ አባባል ኮርጄ “መንግሥትነት ከቤት ይጀምራል” አልሁ። በመሠረቱ ከቤት የማይጀምር ነገር የለም። ከቤት የሚጀምር ነገር በጎም ሆነ ክፉ በውጭም ይታያል። ከቤት ያልጀመረ ከውጭ አይመጣም። ስለዚህ የብዙ ነገሮች መሠረት ቤት ነው። የሰው ዕድገት የሚጀምረው ከቤት በመሆኑ ቤታችን በኛነታችን ላይ ያለው ተፅዕኖ ቀላል አይደለም። “እናቷን አይተህ ልጅቷን አግባ” መባሉም ለዚህ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጣራው ለሚያፈስ ቤት፤ የወለል እድሳት

ይገረም አለሙ

ጣራው የሚያፈስ ቤት
ጣራው ለሚያፈስ ቤት፤ የወለል እድሳት

መላ አከላቷን ዝንጀሮ እሾህ ወግቷት

መቆም መራድ መቀመጥ ተስኖአት

የትኛውን እንንቀልልሽ ብለው ቢጠይቋት፣

ብታስቀድሙልኝ የመቀመጫየን

እኔ እነቅለዋለሁ ቁጭ ብዬ ሌላውን፣

በማለት መለሰች

ቅድሚያ የሚሰጠውን ነገር ስላወቀች።

ጣሪያው በሚያፈስ ቤት ውስት እየኖሩ ክረምት በመጣ ቁጥር እየተሰቃዩ በጋ ሲሆን የወቅት መለዋወጥ የተፈጥሮ ባህርይ መሆኑ ተዘንግቶ ነገር አለሙን በመርሳት ወለሉን ቢያድሱት ግድግዳውን ቀለም ቢያብሱት አይቀሬ ነውና ክረምት ሲመጣ የሚሆነውን አስቡት፤ ከንቱ ልፋት አጉል ብክነት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ይድረስ ለአርበኛው ጸሐፊ ዕዝራ አስቻለው ዘለቀ

ግርማ በላይ

በተከታታይ የጻፍካቸውን ሁለት ግሩም መጣጥፎች በፍቅር አነበብኳቸው። በነዚህ ጽሑፎች እንደተረዳሁት ጥሩ አንባቢ ነህ፤ የብዕር አጣጣልህም ውብ ነው። አገርህንም እንደምትወድ በጽሑፍህ ብቻ ሣይሆን በረሃ መውረድህ ራሱም በቂ ምሥክር ነው። ማቄን ጨርቄን ሳትል ለአንዲት እናትህ ኢትዮጵያ ስትል እያሳለፍከው ያለኸውን መከራና ስቃይ መረዳት እችላለሁና የእምዬ አምላክ ይከተልህ። አንተን ብቻም ሣይሆን ለተመሳሳይ በጎ ዓላማ የተሰለፋችሁትን ጓዶችህንም ሁሉ ፈጣሪ ይጠብቃችሁ፤ ያሰባችሁትንም ያሳካላችሁ። በረከቱ የሁላችንም ነውና። እኛም በጸሎት ከጎናችሁ አለን።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አስቸኳይ ማሳሰቢያ ለአማራ ምሁራንና ለአማራው በዲያስፖራ

በእውቀቱ ዘኢትዮጵያ

በአሁኑ ወቅት የአገራችን የኢትዮጵያ ሁኔታ እጅግ አስቸጋሪ የሆነበትና የአገራችንም ህዝብ ከባድ መከራና ፍርሃት ውስጥ የተዘፈቀበት ሁኔታ ላይ ደርሰናል፤ የአገሪቱ ሁኔታ ከፍተኛ ሥጋት ላይ መሆኑን ለችግሩ ዋና ምክንያት የሆኑት የወያኔ ገዢዋች እንኳን ሳይቀሩ አገሩ በእሳት ሊቃጠል እንደሚችል በግልፅ እየተናገሩበት ያለ ጉዳይ ነው። ይህ ሁኔታ አገርን በሚጎዳ መንገድ እንዳይሄድ ለማድረግ የምሁራን ድርሻ በጣም ከፍተኛ መሆን ይገባዋል። የአማራውና የኦሮሞ ህዝብ ያነሱት የፍትህና የእኩልነት ጥያቄዋች በአገሪቱ ገዢዎች መሀከል ዘንድ ከፍተኛ ትርምስ የፈጠረና ሁኔታውም በየት አቅጣጫ እንዲሚሄድ ለማወቅ በሚያስቸግር በመንታ መንገድ ላይ እንገኛለን። የኢትይጵያ ህዝብም የወያኔ የእሳት ማገዶ እንዳይሆን ትልቅ ሥራ ከፊት ለፊት ተደቅኗል። በአማራው ህዝብ ላይ የተፈፀመውና በመፈፀም ላይ ያለው ከባድ ግፍና መከራ በአማራው ህዝብ ውስጥ ኃይለኛ ብሶትን ፈጥሯል። ነገር ግን ይህ ብሶት ወደ በጎ ድል እንጂ ወደ ሽንፈት እንዳይሸጋገር ትልቅ ሥራ ያስፈልገዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአቶ አሰፋ ጫቦ ሞት ጉዳይ ምን ደረሰ?

ወለላዬ ከስዊድን

Assefa Chabo
አቶ አሰፋ ጫቦ

አቶ አሰፋ ጫቦ ከአርባ ዓመታት በላይ ከዘለለው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዳይ ውስጥ ጎልተው የታዩ ሰው ነበሩ። እንዲሁም ሊጽፏቸው የፈለጓቸውን ነገሮች የራሳቸው በሆነ የአፃፃፍ ስልት የሚያቀርቡ፣ ስለነበሩ በዚሁ ሥራቸው በብዙዎች ዘንድ ሞገስና ውዳሴ አትርፈዋል። በቅርቡም የትዝታ ፈለግ የሚባል መጽሐፍ አሳትመው ሕዝብ እንዲያነበው አድርገዋል።

የዚህ ጽሁፍ ዓላማ በአቶ አሰፋ የፖለቲካ ሕይወት ወይም ስነጽሁፋቸውን ለመቃኘት ሳይሆን የአሟታቸውን ሁኔታ በተመለከተ ቬሮኒካ መላኩ ባቀረቡት ጽሑፍ ላይ ተመርኩዞ የተነሳ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዘፈንና የሙዚቃ ኮታችን እንኳን አይጠበቅልንም?

ምሕረት ዘገዬ (ከአዲስ አበባ)

Ginbot 20
የግምቦት 20 የሙዚቃ ምርጫ። (ምስል ቅንብር፣ ኢዛ)

ይህ በዓል የማን እንደሆነ አሁን ገና በደምብ ገባኝ! “ኢሕአዲግ” የሚባለው የሕወሓት መሀል-አገራዊ የሠርክ መጠሪያም የለየለት ቅጥፈት መሆኑን በዛሬዋ አጋጣሚ ይበልጥ ተገነዘብኩ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሁለት የኢትዮጵያ ሴት ሯጭ ስፖርተኞች በኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ያሳዩት ጋጠወጥ ባሕሪና ፖለቲካዊ ምርጫ!

ጌታቸው ረዳ

ባንዲራ፣ ሰንደቅ ዓላማ
የትኛው ነው የሚወክለን?

ይህ ትችት የኔን ጽሑፍ በሚያስተናግዱ እንደሚለጠፍ ባውቅም፤ ለሌሎቹ ተቃዋሚ ድረገፆች በሙሉ ተልኳል። ቢያወጡት አስተማሪ ነው። ብዙዎቹ ግን እንደማያውጡት ጥርጣሬ አለኝ። ምክንያቱም የፖለቲካ መሪዎቻቸውና ድርጅቶቻቸውን ጨምሮ በዚህ ትችት ስለተካተቱ ወገንተኛነታቸው ከሉጓም በበለጠ ይስባቸዋል። ለማንኛወም ለታሪክ ልኬአለሁ።

አሁን ወደ ርዕሱ ልግባ። በትግርኛ በምንመስለው ምሳሌ ልጀምር፡ {ዝፀገባ ደራሁስ ምስ ፀኻድም ማሕበር ይኣትዋ}  “የጠገቡ ዶሮዎች ከጭልፊቶች ጋር ማሕበር ይገባ”፡ ይባላል። ሁለቱ ዓለም አቀፍ የሴቶች እውቅ ሯጮች ከጭልፊቶች ጋር ማሕበር መግባቱ ምርጫቸው አድርገዋል። ይሆናል።የጭልፊቶቹ እና የዶሮዎቹ ማሕበር የሚቆየው ዕድሜ አብረን የምናየው  ይሆናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ