አሁንም፤ ኤርትራ መዳኛችንም መጥፊያችንም ትመስላለች

አለቃ ተክሌ ቫንኩቨር-ኦታዋ (ካናዳ)

ኤርትራ፣ አርበኞች ግንባር፣ ግንቦት ሰባት

የዛሬው ንባባችን ትንሽ መንገጫገጭ ሊበዛበት ስለሚችል ቀበቷችሁን አጥብቁ። ግንቦት ሰባት የምወደውና የምሳሳለት ድርጅት ነው። ለግንቦት ሰባት መቆም የገንዘብና የሀሳብ ካስማና ምሰሶ ካቀበሉት ሰዎች አንዱ ነኝ፤ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ፤ ክፍያ የፈጸምኩባቸውን ደረሰኞች ላሳይ እችላለሁ። በዚህ ዘመን በኛ እድሜ በቀጣዮቹ ጥቂት አመታት ውስጥ ኢትዮጵያ ውስጥ በአመጽ ለውጥ መምጣት ካለበት፤ ቢከፋም ቢለማም ያንን የማሳካት አቅም ያለው ግንቦት ሰባት ብቻ ነው ባይ ነኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

… ከዚኽ ወዴት? (ክፍል አምስት - አያልሰው ደሴ)

የኢትዮጵያ ህዝብ፣ አገር ወዳድና ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች እና ኢህአዴግ ከዚኽ ወዴት? ክፍል አምስት (ከክፍል አራት የቀጠለ)

አያልሰው ደሴ (የግል አስተያየት)

ሐ-፩፦ የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ቅንጅት (ኢዴኃቅ)

በአገራችን የተደራጀ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ታሪክ የተለያዩ ፖለቲካዊ አመለካከቶችና ፍልሥፍናዎችን የሚከተሉ፣ አልፎም ተፃራሪ አስተሳሰቦችን የያዙና በተመሳሳይ የፖለቲካ ቅኝት ውስጥም ሆነው ነፍስ እስከመጠፋፋት በደረሰ ሁኔታ በምር ጠላትነት የተፈራረጁ የፖለቲካ ድርጅቶችን በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ ከማስቀመጥ አልፎ በጋራ ለመታገል ቆርጠው የጋራቸው የሆነ ድርጅት መሥርተው በአንድነት የታገሉበት የመጀመሪያው የጋራ የትግል መድረክ የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ቅንጅት (ኢዴኃቅ) ነው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ምነው ልጅ ተክሌ ጥምረትን ጠመዱ - ውህደትን ወደዱ?

አዜብ ጌታቸው

ከጥቂት ቀናት በፊት ልጅ ተክሌ ከካናዳ "ያጣነው ጥምረት አይደለም ድፍረት ነው" በሚል ርዕስ የአፋራ ህዝብ ፓርቲ፣ ግንቦት ሰባት እና የኢትዮጵያ ህዝብ የአንድነትን የፍትህ ንቅናቄ ጥምረት መመስረታቸውን አስመልክተው ያቀረቡልንን ጽሑፍ ያነበብኩት በጽሞና ነው። በርካታ ነጥቦችን የዳሰሰ ማለፊያ ጽሑፍ ነው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ማስታወሻ ለልጅ ተክሌ (ታደሰ ብሩ)

ጥምረትን በተመለከተ ጥቂት ነጥቦች

ታደሰ ብሩ

መንደርደሪያ:- ልጅ ተክሌ "ያጣነው ጥምረት አይደለም፤ ድፍረት ነው" በሚል ርእስ በጻፈው ተገርሜም አዝኘም አልወጣ ስላለኝ ጥቂት ማለት ፈለኩ። በተደጋጋሚ ሙከራዎች ስላልተሳኩ ትብብር፣ ህብረት፣ ግንባር፣ ቅንጅት እና መሰል ቃላት ሁሉ የቫንኩቨሩን ልጅ ያንገሸገሹት ይመስላል።  (... ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ! ...)

ሳያዩ የሚያምኑ፤ ሳይሰሙ የሚያወሩ፤ ... (አሥራደው)

ሳያዩ የሚያምኑ፤ ሳይሰሙ የሚያወሩ፤ ሳይናገሩ የሚኖሩ ብጹአን ናቸው ርሃብን ይቸራሉና!

አሥራደው - ከፈረንሣይ

አዲሱ ዓመት ... አልልም ይልቁንም፤ አዲሱ አመት ያበጠ የሚፈነዳበት፤ የከረረ የሚበጠስበት፤ የጠገቡ የሚራብበት፤ የበደሉ የሚክሱበት፤ እውነት የምታሸንፍበት፤ የሀገር ሀብት የዘረፉ የሚዳኙበት፤ በስልጣን የባለጉ የሚቀጡበት፤ የህግ የበላይነት የሚሰፍንበት፤ ህዝብ የሚከበርበት፤ በግፍ የታሰሩ ነጻ የሚወጡበት ይሁንልን ብል ይሻላል። (... ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ! ...)

ይድረስ ለአቶ ግራማ ካሣ (ታምራት ታረቀኝ)

”በወዳጅህ ላይ ክፉ አትስራ፤ እርሱ ተማምኖ ከአንተ ጋር ተቀምጦ ሳለ” (መጽሐፈ ምሣሌ 3፤29)

ታምራት ታረቀኝ

አቶ ግራማ ካሣ ማንን እንደሚሞግቱ ለምንስ እንደሚሟገቱ የሚያውቁ አይመስልም። በሌሎች የሚሰጡ አስተያየቶችን በቅጡ አንብበው ጭብጡን ተረድተው ሊጽፉ ቀርቶ ከራሳቸው ሃሳብ ጋርም በወጥነት የሚዘልቁ ላለመሆናቸው አንድ ሁለት ጽሑፎቻቸውን ማየት ብቻ ይበቃል። በቀናት ልዩነት የሚጽፉት ቀርቶ በአንድ ቀን የሚጽፉዋቸው ሳይቀር እርስ በርስ የሚቃረኑ ለመሆናቸው ጽሑፎቻቸው ይመሰክራሉ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ነብይ በአገሩ አይከበርም” … እውነት!? (ማስተዋል አዳነ)

ክፍል አንድ (ማስተዋል አዳነ)

ጊዜው በአገራችን ክረምት ሊገባ ጥቂት ጊዜያት የቀሩበት ወቅት ነበር፤ የአሁኑ ክረምት። ወደአገር ቤት ለመሄድ የወሰንኩት ቤተሰብ፣ ጓደኛና ዘመድ ለመጠየቅና በአጠቃላይ የአገራችን የኑሮ ሁኔታ በጣም ስለናፈቀኝ፤ ይህንን ደግሞ ከተወሰነ አመት የትምህርት ቆይታ በኋላ ተመልሼ ማየት አለብኝ የሚል ውሳኔ ላይ ስለደረስኩ ነበር። ተማሪ ስለሆንኩና የእረፍት ጊዜዬንም በዚሁ አጋጣሚውን መጠቀሙ ጥሩ አማራጭ ስለሆነ ከፍራንክፈርት ወደአዲስ አበባ ትኬት ቆርጬ ግንቦት መጨረሻ ላይ ወደአገር ቤት ለመሄድ ተሰናዳሁ። የበረራ ቀን ሰኞ ነበር። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ያጣነው ጥምረት አይደለም ድፍረት ነው

ትብብር፣ ሕብረት፣ ግንባር፣ ቅንጅት፣ መድረክ፣ አሁን ደግሞ ጥምረት

ልጅ ተክሌ (ቫንኩቨር-ካናዳ)

አንዱ ይሄ ቀጥዬ የምተቸው ክስተት የማይጥመው ወዳጄ፡ “ትብብር መጣ፡ ሕብረት መጣ፡ ቅንጅትም መጣ፡ መድረክም መጣ፡ እነሆ አሁን ደግሞ ጥምረት መጣ፡ እንግዲህ የቀረው ድብልቅ” ነው ብሎ ተሳለቋል። ከዛሬ ነገ አስመራ ገብቶ የግዞት መንግስተ ያቋቁማል ወይም አንዱን የሕወሀት ሚኒስትር አፍንጫውን ይለውና አንጀታችንን ያርሳል፤ እንደው ሌላው ቢቀር ባለበት ሆኖ በድፍረት እኛ ነን እንጂ እናንተ መንግስተ ልትሆኑ አይገባችሁም ብሎ ይናገራል ብዬ ስጠብቅ በዚህ ጊዜ አለን የምንለው ጠንካራው የፖለቲካ ድርጅት ግንቦት ሰባት፣ አንዱን ግንባር ወይም ትብብር በቅጡ ሳናጣጥም ሌላ ጥምረት የሚባል ፍጥረት ይዞ ሲድህብን በጣም ተበሳጭቻለሁ። እኔ ጸረ-ፓርቲዎች-ጥምረት ነኝ። የስራ እንጂ የፕሮግራም ትብብር አይመቸኝም። ሙሉውን አስነብበኝ ...