የያያ አባቦር፣ የበፈቃዱ ሞረዳ እና የተስፋዬ ገብረአብ አስተያየቶችና ምልልሶች

የጋዜጠኛው ማስታወሻ Yegazetegnaw Mastaweshaተስፋዬ ገብረአብ Tesfaye Gebreabበ”ናፍቆት ኢትዮጵያ” መጽሔት ላይ ያያ አባቦር ”’የአደአው ጥቁር አፈር’ ጋዜጠኛ ወይስ የፓርቲ ካድሬ?” በሚል ርዕስ ያስነበቡትን ጽሑፍ ተከትሎ አሁን በሰሜን አሜሪካ በስደት የሚገኘው የ”ጦማር” ጋዜጣ ባለቤትና ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ በፈቃዱ ሞረዳ ”እኔም ማስታወሻ አለኝ” በሚል ርዕስ በዛው መጽሔት ላይ የበኩሉን ብሏል። ጋዜጠኛና ደራሲ ተስፋዬ ገብረአብ ደግሞ በኢትዮ ሚዲያ ፎረም ላይ በዚህ ሣምንት ”የግንቦት ማስታወሻ” በሚል ርዕስ አንድ ጽሑፍ አስነብቧል። ሦስቱም ፀሐፊዎች ያስነበቧቸው ጽሑፎቻቸው ተያያዥነት ያላቸውና እርስ በእርሳቸው ምላሽ የተሰጣጡባቸው ሆነው ስላገኘናቸው የሦስቱንም ፀሐፊዎች ዕይታና አስተያየት አቅርበናቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የግንቦት ማስታወሻ (ተስፋዬ ገብረአብ)

ጋዜጠኛና ደራሲ ተስፋዬ ገብረአብ Tesfaye Gebreabከተስፋዬ ገብረአብ (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.)

እነሆ! ዛሬ ቅዳሜ ነው።

ዕለቱም ግንቦት 9፣ 2009።

ትናንት ደግሞ ግንቦት 8 ነበር። በአበሻ የዘመን አቆጣጠር ልክ የዛሬ ሃያ ዓመት ግድም ”ጥቂት ጄኔራሎች” ኮሎኔል መንግሥቱ ላይ የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ አድርገው ነበር። ሳይሳካላቸው በመክሸፉ ዛሬ በሕይወት የሉም። ማንኛውም አጥንት - አስከሬን ሆነዋል። አምላክ የጄኔራሎቹን ነፍስ ይማር። እኒያ ሰዎች ከነሙሉ ችግራቸው ከኮሎኔል መንግሥቱ የተሻሉ ዜጎች ነበሩ ብዬ አምናለሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እኔም ማስታወሻ አለኝ (በፈቃዱ ሞረዳ)

የጋዜጠኛው ማስታወሻ Yegazetegnaw Mastaweshaከበፈቃዱ ሞረዳ

ቀድሞው የጋዜጣችን ተወዳጅ አምደኛ፤ የዛሬው እንደኔው ስደተኛ ያያ አባቦር፤ ”የጋዜጠኛው ማስታወሻ” በተባለው መጽሐፍ ላይ ባለፈው የ”ናፍቆት ኢትዮጵያ” መጽሔት ዕትም ("የአደአው ጥቁር አፈር" ጋዜጠኛ ወይስ የፓርቲ ካድሬ?") ባቀረበው ጽሑፍ መነሻነት ወይንም ተንኳሽነት የተጻፈ ማስታወሻ ነው ይኼ ጽሑፍ። ይህ የእኔ ማስታወሻ የተስፋዬ ገብረአብን ማስታወሻ ሥነጽሑፋዊ ወርድና ስፋት የመመርመር ተልዕኮ የለውም። ዕይታው ወዲህ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

”የአደአው ጥቁር አፈር” ጋዜጠኛ ወይስ የፓርቲ ካድሬ? (ያያ አባቦር)

Yegazetegnaw Mastawesha የጋዜጠኛው ማስታወሻያያ አባ ቦር - ከሂዩስተን

ባለፉት 48 ወራት ውስጥ ያነበብኳቸውን የአማርኛ መጻሕፍት ሳስብ ሦስት መጻሕፍት በውስጤ ያኖሩት ደስ እስከወዲያኛውም ባይደበዝዝ ደስ ይለኛል። ዘነበ ፈለቀ (የብዕር ስሙ ነው) የፃፈውን ”ነበር”፤ የፕሮፌሠር መስፍን ወልደማርያምን ”የውድቀት ቁልቁለት” እና አንዳርጋቸው ፅጌ የፃፈውን ”ነፃነትን የማያውቅ ነፃ አውጪ” የተሰኙት መጻሕፍትን መጥቀሴ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዐፄ ዮሐንስና ዐፄ ካሌብ ቢኖሩ እንዴት ያዝኑ! (ሕብረት ሰላሙ)

ሕብረት ሰላሙ (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.)

ከጥንቶቹ ጀግኖቻችን፤

እንደሚታውቀው ዐፄ ዮሐንስን እጅግ በጣም ከሚያስደንቃቸውና ከሚያስከብራቸው ታሪካቸው ዋነኛው ለውድ ሀገራቸው ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና ዳር ድንበር መከበር በቆራጥነት ይከላከሉ የነበረውና ሕይወታቸውንም የሰዉለት መሆኑ ነው። የጀግናው የዐፄ ዮሐንስ ራስ ተቆርጦ ሱዳን ከተወሰደ ልክ 120 ዓመት ሆኖታል። እስካሁን አልተመለሰም!

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ተስፋዬ ገብረአብ ይሰቀል? ወይስ ይወደስ? (ልጅ ተክሌ)

ልጅ ተክሌ-ከካናዳ

የትችት ብድር፤

ጋሽ ገዳሙ መኳንንት እና አያ ነአምን ዘለቀ

የጀርመኑ ጋሽ ገዳሙ መኳንንት የምወደው፣ የማከብረው፣ የኢትዮጵያ ጉዳይ እለት እለት የሚያቃጥለው፣ የወያኔ ስራ የሚፈጀው፣ ወደዚህ ወደሀገረ ካናዳ ከመጣሁበትና እሱን ካወቅኩበት እለት አንስቶ ስለኢትዮጵያ ያለው ስሜት የማይዋዥቅ፣ አገር ወዳድ፣ ታላቅ ትሁት፣ የሩቅ የሀሳብ ወዳጄና መምህሬ ነው። ጋሽ ገዳሙ ሲናገር፣ ሲጣራ፣ ሲመሰክር እንዴት ደስ ይላል?። አያውቀኝም። ግን ያውቀኛል። ሲጣራ፡ “ተክልዬ፡ የናቴ ልጅ” ሲል ሆዴ ሽብር ይላል። ለማውገዝና ለመሳደብ አይቸኩልም። ተስፋዬን ግን ጠላብኝ። ኢትዮጵያዊውን ተስፋዬ ገብረአብን ጨከነበት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሰላለፍ እና የፖለቲካ ትብብር ጥያቄ (አምሃ ዳኘው)

አምሃ ዳኘው (የአንድነት ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና የጥናት እና ምርምር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ) This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.  

ይህ ጽሑፍ በታህሳስ ወር 2001 ዓ.ም. መጀመሪያ ላይ ለአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ቀርቦ የነበረ ጥናታዊ ጽሑፍ ነው። አቶ አምሃ ዳኘው የአንድነት ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል እና የጥናት እና ምርምር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ስንት ዘመን … ቴያትር ይስሩብን? (ልዑልሰገድ)

ስንት ዘመን “መፈንቅለ መንግሥት”፣ “ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት ሊናድ …”፣ “ልንገደል ነበር” እያሉ ቴያትር ይስሩብን?

ልዑልሰገድ (ከአቢሲኒያ)  This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

በሥልጣን ላይ ያለው የአቶ መለስ ቡድን በየጊዜው ንጹሃንን ለመግደል ለማሰቃየትና ለማስር የመሰለውን ወንጀል ይፈጥራል። አንዳንዴ ቴአትሩ መልኩን ለወጥ አደረገ ሲባል ሌላ ጊዜ እንዲህ እንደሰሞኑ የተለመደና አስቂኝ የሚሆንባቸው አጋጣሚዎች ሞልተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የግብርናው ነገር እውነታው ሌላ፤ የሚባለው ሌላ (ፕ/ር ሰይድ ሐሰን)

ፕሮፌሠር ሰይድ ሐሰን፤ መሪ ስቴት ዩኒቨርሲቲ (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.)

በመሪ ስቴት ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስና ፋይናንስ ዲፓርትመንት ውስጥ የኢኮኖሚ ፕሮፌሠር የሆኑት ዶ/ር ሰይድ ሐሰን "የግብርናው ነገር እውነታው ሌላ፤ የሚባለው ሌላ” በሚል ርዕስ ባቀረቡት በዚህ ጽሑፍ በኢትዮጵያ ያለውን የግብርና መስክ፣ የመንግሥትን የመሬት ፖሊሲ፣ ድሃው የኢትዮጵያ ገበሬ ያሉበትን ችግሮች፣ በተለይም በኢህአዲግ የሥልጣን ዘመናት የደረሱበትን በደሎች፣ ... በመተንተን የመፍትሔ ሃሳቦችን ጠቁመውበታል። መልካም ንባብ!

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ትኩረታችን የት መሆን እንዳለበት? (አማኑኤል ዘሰላም)

አማኑኤል ዘሰላም This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. (ሚያዝያ 29 ቀን 2001 ዓ.ም.)

ኢትዮጵያ አሁን ላለችበት ሁኔታ፣ የፖለቲካ መሪዎችን ተጠያቂ የሚያደርጉ ጥቂቶች አይደሉም። አንዳንድ ሰዎች “መሪ የለንም!” ብለው እስከመናገርም ይደርሳሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...