ዜና እና ኢትዮጵያ (ባየነው)

ባየነው ከፊንላንድ

በዚህ በኢንተርኔት ዘመን ለሚኖረው ኢትዮጵያዊ በሚቀጥለው ቀን ምን ዓይነት ዜና እንደሚቀርብለት መገመት አይቸግረውም። በቅርቡ በAmerican Chronicle ላይ “Why Europe can not tolerate the existance of 'Ethiopia' “ በሚል ርዕስ በዶ/ር ሙሐመድ ሜጋሎማቲስ የተፃፈው ፅሁፍ '.. the gangster state 'Ethioipia' must be decomposed and broken down to ten pieces, and all the oppressed nations that have been held captive therein must be liberated.' ብሎ ይደመድማል። በርግጥ ከሌሎቹ ፅሁፎቹ እንደተራዳሁት ሰውዬው ፀረ-ኢትዮጵያ (እንደሱ አባባል ኢትዮጵያ የሚለውን ስም እኛ ሰርቀነው ነው) ብቻ ሳይሆን ዘረኝነትንና ጥላቻን፣ ፀረ-ሠላምን የሚያስፋፋ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች (ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም)

መስፍን ወልደማርያም (ፕ/ር)- ግንቦት 2000

ስማቸው እንደሚያመለክተው፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ከመንግሥት መዋቅር ውጭ ሆነው፣ ከመንግሥት ምንም ያህል እርዳታ ሳይፈልጉ፣ ራሳቸው ከየትም በሚሰበስቡት ገንዘብ በአገር ውስጥ የሚሠሩ ድርጅቶች ናቸው። የሚሠሩት ምንድን ነው? የሥራቸው ዓይነት በጣም የተለያየና ሰፊ ቢሆንም፣ በሁለት መመደብ የሚቻል ይመስለኛል። አንደኛው በሰብዓዊ ርኀራኄ ላይ የተመሠረተና የሰውን ልጆች መራራ ኑሮ በተቻለ መጠን ለመቀነስና ወደተሻለ መንገድ ለመምራት ነው። ሁለተኛ የተፈጥሮ አደጋ ወይም ሰው-ሠራሽ ቀውስ በደረሰ ጊዜ አስፈላጊውን እርዳታ ለተጎዱት ሰዎች ለማቅረብ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ስለ ግንቦት ሰባት፣ የሰባት መቶ ሰባ ሰባት አስተያየቶች መባቻ (አባኪያ)

ከአባኪያ

እንደመግቢያ እንደመነሻ

ይሄንን ጽሁፍ እየጻፍኩ እያለ ጓደኞቼ የላኩልኝን በቻይና ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅት ለማቋቋም ሲሞክር ስለታሰረ ሰውና እየተመላለሰች ስለምትጠይቀው እህቱ የሚያትት ጽሑፍ ሳነብ፣ የሚማርክና ከኢትዮጵያ ሁኔታ ጋር የሚመሳሰል ሃሳብ አገኘሁበትና እዚህች መጣጥፍ ላይ ሻጥ ላደርጋት አሰብኩ። ያው የቻይና መንግሥት ክስም እንደ ኢህአዴግ መንግሥት ክሶች ተመሳሳይ ነው። መንግሥት ለመገልበጥ ወይም ለመጣል አሲራችኋል አይነት ነገር። የጽሑፉ አቅራቢ ሴት፣ በዚህ ክስ የታሰረ ሕመምተኛ እስረኛ ወንድሟ በሕክምና አመክሮ ካገር ሊወጣ እንደሚችል የተሰጣትን ምክር ይዛ ምን እንደሚያስብ ብትጠይቀው፣ “I will not leave China unless my freedom of return is guaranteed” (ወደቻይና የመመለስ መብቴ ካልተረጋገጠልኝ በስተቀር አገሬን ለቅቄ አልሄድም) አላት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ግንቦት ሰባት - ጉዳዩ ኢትዮጵያዊነት ነው (ግርማ ካሣ)

ግርማ ካሣ (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.)

ትዝ ይለኛል በጥቅምት ወር 1984 ዓ.ም. አካባቢ ነበር፤ ሁለት ጓደኛምች በቸርችል ጎዳና፣ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ጀርባ በሚገኘው የ”ትግላችን” ኃውልት ጋር ፎቶግራፍ ለመነሳት የቆሙት። (ይህ ኃውልት አሁን ይኑር አይኑር አላውቅም) እነዚህ ወጣቶች፣ የኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ምስል የሚታይበትን ኃውልት አክብረው ሳይሆን እዚያ ቦታ ፎቶግራፍ ለመነሳት የቆሙት፤ ከኃውልቱ በስተግራ በኩል መሬቱ ላይ ተተክለው የነበሩ አበባዎች ማርከዋቸው ስለነበር ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፍትህን ፍለጋ፣ ዳኝነት አሰሳ (አባኪያ)

የአባኪያ ማስታወሻ፤ አባኪያ ተመልሷል**

ትናንት ለጠበቆቻችን፣ ዛሬ ደግሞ ለዳኞቻችን

“ፍትህን ፍለጋ፣ ፍትህን አሰሳ”

“ፍትህን ፍለጋ፣ ፍትህን አሰሳ” የሚቀጥለው የቴዲ አፍሮ ዘፈን አልበም መጠሪያ ይመስለኛል። “ቃሊቲ ቃሊቲ” ሊለውም ይችላል። መቼም ዶ/ር ብርሃኑ ወይም ኢንጂነር ኃይሉ ወይንም ብርቱካን ሚደቅሳ ቢዘፍኑ አያምርባቸውም። ነገር ሁሉ ለበጎ ነው የሚለውን የሐዋርያውን ቃል ካመንበት፤ ምናልባትም የቴዲ አፍሮ መታሰር ለበጎ ነው። ከዚህ ቀደም ጽሑፌን ያቆምኩበትን አልዘነጋሁም። ወደዚያ እመለሳለሁ። ለጊዜው ግን ፈተና ላይ ከርሜ ጠፋሁኝ። ኢትዮጵያ የተውኩትን/ያቋረጥኩትን ትምህርት እዚህ ቀጥያለሁ። ይሄ የጀመርኩትን ትምህርት ምዕራብና ምስራቅ ጫፍ ካላቸው፣ ከምዕራብ ጫፍ ምስራቅ ጫፍ የመሄድ ያህል ዞሬ ነው የጀመርኩት። መቶ ሰማኒያ ዲግሪ መዞር የሚሉት አይነት ነገር። ቀድሞ እማር የነበረው የcivil law ሥርዓትን መሰረት ያደረገውን የኢትዮጵያን ሕግ ነበር። አሁን ወደ common law ዞሬያለሁ። ሕግን - ሕግ ከሚከበርበት ሀገር ስትማሩት እንዴት ደስ ይላል መሰላችሁ። አሁን የምማረው በተለይ እንግሊዝ፣ ካናዳ፣ አውስትራሊያ፣ አሜሪካና ካናዳ የሚከተሉት የሕግ ሥርዓት ቀደም ሲል ምናልባትም ከአንድ ሺህ ዓመታትም በፊት ጀምሮ የተወሰኑ ውሳኔዎችን መሰረት ያደረጉ፣ መርሆዎችና ሕግጋት በተመሳሳይ ሁኔታ ውስጥ ለሚፈጠርና ለሚገኝ ጉዳይ በተመሳሳይ መልኩ የሚወሰኑበት የሕግ ሥርዓት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የማሰር ባሕል (ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም)

Prof. Mesfin Woldemariamመስፍን ወልደማርያም (ፕ/ር) ግንቦት 2000

በጥንቶቹ መሣፍንት ዘመን፣ የአንድ ቡድን የሥራ መሪ ሆኜ ወደ ጎሐጽዮን ኼጄ ነበረ። የማላውቃቸው የወረዳው አስተዳዳሪ የሆኑ አንድ ባላምባራስ፣ መኪና ውስጥ ተቀምጬ ከሰው ጋር ስነጋገር አዩኝና አልወደዱልኝም። “ማነው ይኼ፣ ምንድነው የምታነጋግረው፣ …” እያሉ ሰውየውን ሲቆጡ፣ ከመኪና ወረድኩና ማንነቴን ገለጽኩላቸው፤ ደብዳቤም አሳየኋቸው። ከምመራው ቡድን ውስጥ አንድ አሜሪካዊ አይተዋልና መሪው እኔ ነኝ ስላቸው በጣም ተናደዱ። “ይኼ ደፋር! ፈረንጅ እያለ መሪው እኔ ነኝ ይላል?!” ብለው ወደ ፖሊሱ ዞሩና “ውሰደው፤ እሰርልኝ!” አሉት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የቫቲካን ጥቅም ከኢትዮጵያ ክብር ይልቃል?!

(በኪዳኔ ዓለማየሁ)

ፋሺሽት ኢጣልያን ደግፋ ኢትዮጵያ ላይ ለደረሰው የሰው ዘር እልቂትና ሌላም ከባድ ጥፋት የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እንድትጠይቅ በመደጋገም ተጽፎላት አሻፈረኝ ያለቺው የቫቲካን፤ ካቶሊካዊት መንግሥት፤ ኢትዮጵያ ውስጥ በሰፊው ለመንቀሳቀስ (ለመዝመት ልበለው?) ቆርጣ የተነሳች መሆኑን የሚያመለክቱ ክስተቶች እየታዩ ነው። ለዚህም፤ 1ኛ/ በቫቲካን አማካኝነት አዲስ አበባ ሊከፈት ስለ ታሰበው ግዙፍ የሆነ የካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ እና 2ኛ/ ሰሞኑን ከፕሬዚዳንት ግርማ ጭምር ተገናኝተው ስለ ነበሩት፤ የቫቲካኑ መሪ ፖፕ ቤኔዲክት 16ኛ ልዩ ተወካይ፤ ካርዲናል ዲያስ፤ ኦፊሴልያዊ የኢትዮጵያ ጉብኝት በማስረጃነት መጥቀስ ይቻላል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሰው አገርን በመውረር ምን ይገኛል? (ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም)

መስፍን ወልደማርያም (ፕ/ር)

በዛሬው ጊዜ ዓለም አቀፍ ሕጎች፣ በተለያዩ የአካባቢ ማኅበሮችና በተባበሩት የዓለም መንግሥታት ማኅበር ታትመውና ታውጀው፣ ተሰብከው፣ ብዙ ዲስኩሮችም በታላላቅ ሰዎች በተደጋጋሚ ተደርጎባቸዋል። ከብዙ ዓመታት በፊት ቻይና ቲቤትን ስትውጥ፣ ለጥቂት ጊዜ ተወራና ተረስታ፤ እኛም ካልረሳነው ኢጣሊያ ኢትዮጵያን ስትወር እንዲሁ ነበር፤ ዛሬ እኛም ወግ ደርሶን ከወራሪዎች ጋር መሰለፋችን በሰፊው እየተወራ ነው። አሁን ደግሞ የአውሮፓ ሕብረት “ቲቤት የቻይና አካል ነች” ብሎ ዐወጀ ይባላል። እንግዲህ ወረራ በይርጋ ይጸድቃል ማለት ነው፤ ጉልበተኞች ጨክነው ዘመናትን ካስቆጠሩ፣ ወረራው በይርጋ እንደሚጸናላቸው አዲስ ትምህርት እየተገኘ ነው። አሜሪካ በኢራቅ ስድስተኛ ዓመቱን እያስቆጠረ ነው፤ ስንት ዓመት ይቀረዋል? ሆኖም የአሜሪካ መንግሥት ከህዝብ ፈቃድ ውጭ ጉልበት የለውምና ወረራው በአሜሪካ ህዝብ ትዕዛዝ የሚያበቃበት ጊዜ ያለ ጥርጥር ይመጣል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በጎንደር የሱዳኖችን ጥቃት በተመለከተ (ግርማ ካሣ)

Atsé Yohanesግርማ ካሣ ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. )

(ሚያዝያ 24 ቀን 2000 ዓ.ም. May 2, 2008)

“ዐፄ ዮሐንስ ይዋሻሉ

መጠጥ አልጠጣም ይላሉ

ሲጠጡ አየናቸው በርግጥ

እራስ የሚያዞር መጠጥ”

 

ይህ ለዐፄ ዮሐንስ አራተኛ የተገጠመ ቅኔ ነበር። ሰሙ፣ ዐፄ ዮሐንስ መጠጥ አልጠጣም እያሉ የሚያሰክር መጠጥ ሲጠጡ እንደሚታዩ የሚገልጽ ሲሆን፤ የቅኔው ዋና መልዕክት - ወርቁ ግን የእኝህን ታላቅ ኢትዮጵያዊ የደም መስዋዕትነት ያሳያል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...