ዶ.ር ፍስሃ እሸቱ፣ ሄኖክ የሺጥላ እና ሌሎች የፌስ ቡክ ታጋዩች!

ታፈሰ ወርቁ

አንዷ ያገሬ ሴት ደጋግማ ስታወራኝ ነው አንዱን የፌስ ቡክ ዝነኛ ታጋይ ያወቅሁት። እንዴት እስካሁን እንዳላየሁት ገርሞኝ በስሙ ፈልጌ ገባሁ። ጊዜየን አላጠፋሁም። ዘጋሁት። ካሁን ቀደም እንዴት የፌስ ቡክ ገጼ ላይ እንደመጣ ሳላውቀው ገጭ ብሎ ባገኘው ከፍቼ አይቸው፣ ሰምቼው... ወዲያው ነበር የዘጋሁት። ያኔ ለመጀመሪያ ጊዜ ሳየው፣ ነብያችን ድንገት ተከስተውለት ኖሮ፣ አዲስ ሙስሊም (convert) ሆኖ ነው መሰለኝ፣ ጥቂት የማውቃቸው ሙስሊም የፌስ ቡክ ወዳጆቼ፣ ላይክ አድርገው “ኢንሻላህ! ሱብሃናሁ ወተዓላ ...”፣ “... እንኳን ወደ እውነተኛው እምነት መጣህ ወንድማችን ...” ... ወዘተ የሚሉ ጽሁፎች ገጹ ስር ተኮልኩለው አይቼ ሳምንት ሳይሞላኝ ነው ያቺው ያገሬ ሴት ስትነግረኝ እንደገና ፈልጌ የገባሁት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ማነህ ባለሳምንት? የ“መሪ” ወርተራ

Assefa Chaboአስፋ ጫቦ

እንደመግቢያ

የኦርቶዶክሶች ማኅበር ቤት ወር ተረኛውን ለመመደብ ዳቦ ከተቆረሰና መውጫ ሲቃረብ ሙሴው ይነሳና፤

ማነህ ባለሳምንት?
ያስጠምድህ ባስራ ስምንት
እኔ ነኝ የምትል የቅዱስ ገብርኤል ወዳጅ ይላል።

ገብርኤሉ እንደማኅበራቸው ታቦት ሥም ይቅያየራል። ተራኛው ይቆምና የሚባለውን ብሎ ጽዋውን ይረከባል። ይህ እውደት በየወሩ ቋሚና ቀጣይ ነው። ከልጅነቴ ያስታወስኩት ነው። እዚህም፤

ማነህ ባለሳምንት?
እኔ ነኝ የምትል ሴራ ወዳጅ ማለት የሚቻል ይመስለኛል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሰው ልጅ ክብርና የብሔረሰብ መብት በኢትዮጵያ

Surma

(ኢትዮጵያ ዛሬ) አንድ የውጭ ሰው ይህን ፎቶግራፍ ሲመለከት፤ በሆነች አፍሪካ አገር ውስጥ በባሪያ አሳዳሪው ሥርዓት የተነሳ ፎቶግራፍ ሊመስለው ይችላል። ይህ ግን ትናንት በእኛው አገር፤ በኢትዮጵያ የተፈጸመ ነው።

ልክ የዛሬ ዓመት ነው በደቡብ ክልል ሱርማ ውስጥ መሬታቸውን ለመንግሥት “የሙስና" ፕሮጀክት ለሆነው የስኳር ፕሮጀክት “ያለ ካሣ ከመሬታችን አንነሳም” በሚል የዜግነት መብታቸውን ስለጠየቁ ብቻ፤ እንደ ውሻ አንገታቸው ላይ ገመድ ገብቶ በውርደት እንዲታሰሩ የተደረጉት።

ይህ ፎቶ ብቻውን ኢትዮጵያን እየመራሁ ነው የሚለውን ሥርዓት ለዜጎች ያለውን ክብር እንዲሁም በዜጎች ላይ ያለውን ንቀት የሚያሳይ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያዊ የአማራ ተጋድሎ

ዶ/ር ተክሉ አባተ

YeAmara tegadelo

ከጥቂት ወራት ወዲህ የመገናኛ ብዙኃንን ትኩረ ከሳቡ ወሳኝ ጉዳዮች ውስጥ የአማራ መደራጀት ዋናው ሳይሆን አልቀረም። ይህን ጉዳይ በተመለከተ በርካታ ጽሑፎችና ንግግሮች ተደርገዋል። አማራው እንደ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ነገድ መደራጀትና ራሱን ከተቀነባበረ ጥፋት ማዳን እንዳለበት የሚሞግቱ በርካቶች ናቸው። አሳማኝ የመከራከሪያ ነጥቦችንም አንስተዋል። በአንጻሩ ደግሞ አማራው በኢትዮጵያዊነት እንጅ በነገዱ መታገል መዘዙ ብዙ እንደሆነ ያስጠነቀቁ አሉ። ከሁለቱም ወገኖች አንዳንዶች ነጥቦቻቸውን በምክንያት ወይም በመረጃና በማስረጃ መደገፍ ሲሳናቸው አፍ አውጥተው ሌሎች ጸሐፍትን ሲሳደቡና ”ወያኔ ነህ”፣ ”ፀረ አማራ ነህ” እያሉ ሲያሸማቅቁ ታይተዋል። ከነዚህ ከተሳዳቢዎችና ከአሸማቃቂዎች በስተቀር ለሌሎች ጸሐፍት ከፍ ያለ አክብሮትና ምሥጋና አቀርባለሁ። መሠረት ያላቸው ውይይቶችና ክርክሮች ለሚደረገው ትግል ግልጽነትንና መናበብን ይፈጥራሉና!

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የእሳት እራት ራሷን ለመታደግ ቀለሟን ቀየረች

Mareshet Mesheshaማርእሸት መሸሻ

ታላቁ የዝግመተ ለውጥ (evolution) ሳይንቲስት ቻርለስ ዳርዊን የነፍሳት ሥነ ነገር (Origin of Species) በተባለው ምርምሩ ላይ የቀመረው ታሪክ አለ። ይህም አንዲት የትንሽ እሳት እራት ዘር (the peppered moth) በህልውናዋ ላይ የተደቀነባትን ድንገተኛ አደጋ እንዴት አድርጋ እንደተወጣችው የሚተርከው ነገር ነው። እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ1880ዎቹ ዓመታት የተቀሰቀሰው የኢንዱስትሪ አብዮት (industrial revolution) ብዙም ሳይውል ሳያድር የታላቋን ብሪታንያ ገጠር በውበት አልብሶት የነበረውን፤ ቀለሙ ነጣ ያለ ቅጠል የሸፈነው ደንና ጫካ ከየፋብሪካው የተነነው ቆሻሻ ተመልሶ ወደ ህዋ መጥቆ፣ ወደ መሬት ዝናብ ሆኖ ተመልሶ ወርዶ፤ አገሪቱን በጥቅርሻ አለበሳት። ደንና ጫካው ቅጠሉ ነጣ ያለ በነበረበት ጊዜ የምርምሩ አርዕስት የሆነችው እሳት እራት የነበራት ቀለም ነጣ ያለ ነበረ። ከመኖሪያዋና ከአካባቢዋም የሷም ቀለም በመዋሃዱ ምክንያት ራሷን ከወፍ ዕራት ለመሆን አድኗት ነበር። ቅጠሎች በጥቅርሻ ሲሸፈኑ ግን በድንገት ተጋለጠች። ከአካባቢዋ ቀለም የእሳት ራቷ ቀለም ነጥቶ በመታየቷም አዳኝ ወፎች በቀላሉ ይለቅሟት ጀመር። ዘሯ በሙሉ ህልውናው ለአደጋ ተጋለጠ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በገዛ ዳቦዬ

Assefa Chaboአስፋ ጫቦ

ዛሬ በሌላ ሰበብ በጨረፍታም ቢሆን ለማየትና ለማሳየት የምሞክረው አሜሪካ ኗሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያን በንግዱ ዘርፍ ተሳታፊነት ነው። ዲያስፖራ አላልኩም! ቃሉን ስለማልወደው ነው! ሌላ ቀን እንወያይበታለን!

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመሸበት ማደር!

አስፋ ጫቦ

Prof. Merera Gudina in jail

“እውነቱን ተናግሮ የመሸበት ማደር!” የሚል አባባል አለ። ወዳጄን ዶክተር መረራ ጉዲናን ሳስታውስ ያ አባባል ይመጣብኛል። ከዚያ የተሻለ ሊገልጸው የሚችል አባባል ሊኖር ይችላል። አልመጣልኝም! አሁን ታሰረ! በዚያ ምክንያት ነው ይህንን የምጽፈው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከፍተን ብናየው? የሻዕቢያና የኦነግ መስተፋቅር

Assefa Chaboአስፋ ጫቦ (ዳላስ፣ ቴክሳስ)

እንደመግቢያ

ዛሬ ትንሽ መጻፍ የፈለኩት በኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) እና በኢሳይያስ አፈወርቂ መካከል ያለውን የቆየ ጥብቅ ትስስር በመጠኑ ለመፈተሽ ነው። መነሻ የሆነኝ እንግሊዝ አገር ሎንዶንና አሜሪካ፤ አትላንታ፣ ጆርጂያ የኦሮሞ “ምሁራንና ብሔርተኞች” ያደርጉት ስብሰባና የሰጡት መግለጫ ነው። ያ ራሱን ችሎ መነገር ያለበት ስለሚመስለኝ እመለስበታለሁ። የዚህኛው ዓላማ እዚያ ሰበሰባ ላይ ተካፋይ ከነበሩት “ነፃ አውጭዎች” አንዱን ኦነግን በጨረፍታ ለመታዘብ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የነጻነት ቀን እስትንፋስ

የትነበርክ ታደለ

Gambia election 2016

"ነጻነትን እንደ ዛሬ አይቻት አላውቅም!" አንድ ጋምቢያዊ የተናገረው ነው። 22 ዓመት ሙሉ በውስጡ የተሸከመው መርግ ልክ ረዥም ርቀት በጀርባው ኩንታል ተሸክሞ ማውረጃው ሲደርስ ሸክሙን 'ድብ' አድርጎ ወርውሮ እፎይ እንዲል አዲስ የነጻነት ትንፋሽ እየተነፈሰ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኦሮምኛ ግዕዝ ፊደላትን ስለመጠቀም ተገቢነት

አብርሃም ቀጄላ (ከዋሽንግተን ዲሲ)

Oromiffa in Geez

በርካታ በአገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተደረጉ ጥናቶች አሁንም ዛሬ በግዕዝ ፊደል መጠቀም ቀላልና ለሕዝብ ሳይኮሎጂካል፣ ማኅበራዊና ብሔራዊ ማግባባት እንደዚሁም ለመጭው ትውልድ አብሮነት ተወዳዳሪና መተኪያ አማራጭ የሌለው መፍትሔ መሆኑንና፤ ይኼው እንዲፈጸም በበርካታ መረጃዎች እያስደገፉ በማስረዳት ላይ ይገኛሉ። አሁን ላይ ሆነን በዛሬ መስተዋት ያንን የጨለማ ጊዜ ስናየው እንዴት የሚያሳፍር ሁኔታ ውስጥ ማለፋችንን ቁልጭ አድርጎ ያሳየናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ