በትምህርት (ውስጥ) እንደሚገኝ ያለ ድንቁርና የትም የለም!
ተሻለ መንግሥቱ
ከኢትዮሚዲያ ድረገጽ ያገኘሁትን አንድ በፈረንጅ አፍ የተጻፈ መጣጥፍ ይዤ ሳነብ የንባብ ፍላቴን ማረከውና ዘለቅሁት። በዚያም አልበቃኝም። እዚያው መጣጥፍ ውስጥ በተጠቆመ ማስፈንጠሪያ (ሊንክ) ወደ ኢካድፎረም ድረገጽ አመራሁና በዶክተር ተድላ ወ/ዮሐንስ የተጠቀሰውን የፀጋየ አራ አርሳ ፌስቡካዊ ንግግር የተተቸበትን የራሱን የተድላን ትንሽ ቆየት ያለ የሚመስል ጽሑፍ አነበብኩ ... አነበብኩ እንኳን ሳይሆን በንዴት ተቃጠልኩ ነው ማለት ያለብኝ - ለነገሩ እንዲህ ዓይነት የታሪክና የትውልድ ጭንጋፎች በአነስተኛው የሚፈልጉት እንዲህ ዓይነቱን የዜጎችን በንዴት መንጨርጨር ነው። ወፍ ዘራሾች አዕምሯዊ ሥሪታቸው ወይም የአስተሳሰብ ቀመራቸውና ነገረ ሥራቸው ሁሉ ግራ በመሆኑ የሚያስደስታቸው የሚያሳዝን ነገር ነው። ያን ጽሑፍ ስጨርስ ነው እንግዲህ በመግቢያየ ባስቀመጥኩት ርዕስ የተሰማኝን እንደወረደ ለማስቀመጥ ብዕር ያሳሁት። ይህን ግን ያዙልኝ፡- እንደኢትዮጵያ የተረገመ አገር የለም!!!
ሙሉውን አስነብበኝ ...







