የኦሮሞ ብሔረሰብ ቁጥር 31 ሚሊዮን፣ 7 ሚሊዮን ወይስ 50 ሚሊዮን?!

ፈቃዱ በቀለ (ዶ/ር)

መግቢያ
ያለፉትን 40 ዓመታት ፖለቲካችንን ለመረመረ አገርን በሚመለከት የሚሰነዘሩት አስተያየቶች ወይም የሚሰጡት ትንተናዎች ሁሉ ሳንይሳዊ ይዘት ይኑራቸው አይኑራቸው የሚጠይቅ የለም። በተለይም ፖለቲካ ፍልስፍናዊ መሰረት ያለው ታላቅ ፅንሰ-ሃሳብ መሆኑ ግንዛቤ በሌለበት አገርና፣ ማንኛውም ሕብረተሰብንና የአገርን አጠቃላይ ሁኔታ በሚመለከት ረገድ የግዴታ ሳይንሳዊ ትንተና መስጠት አስፈላጊ መሆኑ ቀርቶ ስሜት ዋናው መመሪያ በሆነበት አገር የሚሰነዘሩ አስተያየቶች ትክክል መሆናቸውንና አለመሆናቸውን ቁጭ ብሎ በሰከነ መንፈስ ለመመርመር የሚቃጣ ሰው በፍጹም የለም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እውነተኛ ማዳበሪያና ልማት የራቀው የኢትዮጵያ ማሳ

የትነበርክ ታደለ

King Mohammed VI and PM Hailemariam

ሰሞኑን የሞሮኮው ንጉሥ ወደ አገራችን ጎራ ማለታቸው አንድ አዲስ ዜና እንድንሰማ አድርጎናል። ንጉሥ መሐመድ ስድስተኛ ከኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር የ2.4 ቢሊየን ዶላር ስምምነት ተፈራርመዋል። የ2.4 ቢሊየን ዶላር የማዳበርያ ፋብሪካ ለማቋቋም ነው ስምምነቱ። ጠቅላላ ኢንቨስትመንቱ 3.7 ቢሊየን ዶላር ይደርሳል ነው የተባለው። እ.ኤ.አ. በ2022 ሲጠናቀቅ በዓመት 2.5 ሚሊየን ቶን ማዳበርያ የሚያመርተው ይህ ፋብሪካ የአገሪቱን የማዳበሪያ ፍላጎት ያሟላል ተብሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በዶክተር ፀጋየ አራርሣ “De-Amharicization” ቃል ላይ የሚሰማኝን ልበል?

ማስተዋል በለጠ

ሰሞኑን በኢትዮጵያውያን መሃል የገባብን ወያኔያዊ ንፋስ ደግሞ ከሌላው ጊዜ ለየት ይላል። ከአንዱ ንትርክ ወጣን ስንል ሌላ ይተካል፤ “መቃቃርን አስወገድን፤ ወደ አንድነትም መጣን” ብለን ከመደሰታችን በአንዱ አቅጣጫ የካብነውን የሚያፈርስ ነገር ብቅ ይላል። ከለንደኑ የኦሮሞ የሕግ ምሁራን ስብሰባ ወዲህ እስከ አትላንታው የዚያው ስብሰባ ቀጣይ ክፍል ድረስ እየታዬና እየተሰማ ያለው ነገር ደግሞ ለብዙዎቻችን እምብዝም የሚጥም አልሆነም። ይሁንና ነገር ሁሉ ለበጎ ነው እንዲሉ ብዙ መረበሽ ያለብን አይመስለኝም። ሁሉም ነገር በጊዜው እየተፍረጠረጠ መውጣቱ ለቁስሎቻችን በአፋጣኝ መጥገግና ማንን ከማን ለይተን መጠጋት ወይ መራቅ እንዳለብን ለማወቅ ይጠቅመናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የልብ ስፔሻሊስት በወህኒ ቤት ለማጣት ተቃርባለች

Dr. Fikru Maru

እንደ ፈረንጆቹ የዘመን አቆጣጠር በ1975 ፍቅሩ ማሩ እናት አገራቸውን ለቀው በስዊድን የስደተኝነትን ሕይወት መምራት ጀምረዋል። በስዊድን ቆይታቸው በልብ ሕክምና ስፔሻላይዝድ በማድረግ ዶክትሬታቸውን የሠሩት ፍቅሩ፣ ረዘም ላሉ ዓመታት በስደተኝነት በተቀበለቻቸውና ባስተማረቻቸው ስዊድን በሚገኘው ኹዲክስቫል ሆስፒታል (Hudiksvall) በሞያቸው ሲያገለግሉና በአገሪቱ ዮኒቨርሲቲዎች ሲያስተምሩ ቆይተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጎሠኛነት በባዶ ሜዳ

Prof. Mesfin Woldemariamፕ/ር መስፍን ወልደማርያም

በተለያዩ የኢትዮጵያ አንገብጋቢ ጉዳዮች ላይ ሁሉ የሚደረገው ውይይትና ክርክር እንደተጠናቀቀ ተቆጥሮ የአማራና የኦሮሞ ጎሠኛነት ትልቁ አንገብጋቢ ጉዳይ እየሆነ ነው፤ (ስለኢትዮጵያ ለማያውቅ ሰው በኢትዮጵያ ውስጥ ከጠሩና ከጸዱ አማራና ኦሮሞዎች በቀር በአገሪቱ ውስጥ ሌላ ሰው ያለ አይመስልም!)። ጎሠኛነት ጉዳያችን ያልሆነው ኢትዮጵያውያን የዳር ተመልካች መሆኑ እየሰለቸን ነው። ምንም እንኳን አማራና ኦሮሞ የተባሎት ጎሣዎች በብዛት ከሁሉም ቢበልጡም ከሰማንያ በላይ የሚሆኑ ጎሣዎች እንደሌሉና በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ቃል እንደሌላቸው ተደርጎ የሚጎነጎነው የሚስዮናውያንና የስለላ ድርጅቶች ታሪክ ለኢትዮጵያውያን ባዕድ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፅንፈኝነት አደጋ

አንተነህ መርዕድ

ኢትዮጵያ እንደ አገር፣ ሕዝቧም ነፃነት እንዳለው ዜጋ ለመኖር ያለው ተስፋ አደጋ ላይ እየወደቀ ያለበት ሁኔታ ምክንያቶች ብዙ ቢሆኑም፤ ፅንፈኝነት ጉልህ ቦታ የያዘ ይመስለኛል። የፅንፈኝነትን ፅንሰ ሃሳብ መተንተን ለባለሙያዎች ልተወውና እንደ አንድ ዜጋ የሕመማችንን ምክንያት አቅሜ በፈቀደው አንድ ነገር ማለት አስገደደኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአማራነት መደራጀት፤ ሌላው ኢትዮጵያዊነትን የማጥፋት ስልት

ይገረም አለሙ

በቅድሚያ መልዕክት፤
ርዕሱን አይተው የጽሁፉን አጠቃላይ መልዕክት በጥሞና አንብቦ ለመረዳት ትእግስት በማጣት የጭቃ ጅራፍ ለማጮህ ለሚጣደፉ ወገኖቼ ለአገር አንድነት፤ ለሀዝብ አብሮነት፤ ለነጻነት ትግሉና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ አንቅፋት እስካልሆነ ድረስ ማናቸውም ሰው በመሰለው መንገድ መደራጀት መብቱ መሆኑን የማምን መሆኔን እወቁልኝ። ይህች አስተያየቴ መጻፌ በአማራነት ለመደራጀት ለምን አሰባችሁ? ለምንስ ሞከራችሁ? ሳይሆን፤ በአማራ ይደራጅ ስም የሚነገር የሚጻፈው ኢትዮጵያዊነትን ብቻ ሳይሆን ቆምንለት የምትሉትንም አማራነት የማይጠቅም ሆኖ ስለታየኝ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለገጽታ ግንባታ የተገነቡ፤ ገጽታ አፍራሽ ሆቴሎቻችን

የትነበርክ ታደለ

Fasil hotel, Addis Ababa

ከኢትዮጵያ ሚሊኒየም መባቻ ጀምሮ የተያዘው አዲስ ልክፍት ገጽታ ግንባታ የሚል ነገር ነበር። ሁሉም ነገር ወደ ገጽታ ግንባታ። ሕንጻውም፣ አስፋልቱም፣ ቀለሙም፣ ዳንሱም፣ ዘፈኑም፣ ውበቱም የሚታየው ነገር ሁሉ የአገሪቱን ገጽታ ስለመገንባት ብቻ እንዲያወራ ይደረግ ዘንድ ግድ ሆነ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአሜሪካ ምርጫው በተስቦ እና በኮሌራ መሃከል ነበር

Clinton and Trumpየአሜሪካ ምርጫ - ዶናልድ ትራምፕ ወይስ ሂለሪ ክሊንተን - ምርጫው በተስቦና በኮሌራ መሃከል እንደመምረጥ ያህል ዐይነት ነው!!

ፈቃዱ በቀለ (ዶ/ር)

መግቢያ
የዛሬ ስምንት ዓመት ባራካ ኦባማ ለፕሬዚደንትነት ምርጫ ለውድድር ሲቀርቡ፣ ከፕሪመሪው ጀምሮ የነበረውን የምርጫው ሂደት እዚህ አውሮፓ ሆነን በየሰዓቱ ሁኔታውን በጥብቅ እንከታተል ነበር። በማያጠራጥር መልኩ የብዙዎቻችን ፍላጎትና አድልዎ ለባራክ ኦባማ ቢሆንም፤ ባራክ ኦባማ ያንን አስቸጋሪ የፕሪመሪ ውድድር አልፈውና ተፎካካሪዎቻቸውን አሸንፈው የዲሞክራቲክ ፓርቲውን በመወከል ለፕሬዚደትነት ምርጫ ይቀርባሉ ብሎ የገመተ አልነበረም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአማራ ተጋድሎ ከዚህ ወዴት? (ክፍል ፪)

ሙሉቀን ተስፋው

1. ምን አጣን?

እስካሁን ባካሔድነው ትግል በጣም ብዙ ወንድሞቻችንና እህቶቻችንን አጥተናል። የአማራ እናቶች ዳግም ምርር ብለው አዝነዋል፤ አልቅሰዋል። ሕጻናትና ወላድ እናቶች ሳይቀሩ አማራ በመሆናቸው ብቻ ተጨፍጭፈዋል። በሺሕ የሚቆጠሩ የአማራ ልጆች በየአካባቢው በሚገኙ እስር ቤቶችና የማሰቃያ ቤቶች ታጉረው የወያኔ ቶርቸር ሰለባ እየሆኑ ነው። መተማ ውስጥ በርካታ አማሮች በጅምላ ተጨፍጭፈዋል። እንደበለጠ ንብረቱ ቸኮለ ያሉ ብሩህ አዕምሮ ያላቸውና የአማራ ሕዝብ ተስፋ የሆኑ ወንድሞቻችን በአነጣጥሮ ተኳሾች ተገድለዋል። አሁንም በአማራ ክልል በየቀኑ ልጆቻችን ይገደላሉ፤ ይታሰራሉ። ከዚህም አልፎ የአማራ ተጋድሎ ያርበተበተው ወያኔ፣ በአማራና በሌሎች ሕዝቦች መካከል ግጭት ለመፍጠር ከአማራ ክልል ውጪ በሚኖሩ አማሮች ላይ መጠነ ሰፊ ዘመቻ ከፍቶ እያሰቃያቸው ይገኛል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ