ትዝታ ነው የሚርበን?

አስፋ ጫቦ

Ato Assefa Chabo. አቶ አስፋ ጫቦ

ትዝታ ነው የሚርበን

ላናገኘው ላይጠግብን ብሏል ወዳጄ የነበረው ጸጋዬ ገብረ መድኅን

ለመሆኑት ትዝታ ምንድነው? ዘፈፍን ነው? እንጉርጉሮ? ኩርኮራ? ማላዘን?ሐሳብ ልጓም የለውምና እንዳሻው ወደላይ ወደታች፤ ወደውስጥ ወደውጭ፤ ወደፊት ወደኋላ፣ ወደየሚታይ ወደሊታይ ወደማይቻል ይሔዳል፤ ይጓዛል፤ ይተናል፤ ይበናል፤ ይመላለሳል፣ ይመለሳልም። “ማን አለኝ ከልካይ!” መሆኑ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሄነከን ቢራ ዘረፋ ምስጢር በኢትዮጵያ ሲጋለጥ

ክንፉ አሰፋ

Heineken ethiopia

የሆላንድ ዜምብላ[1] ጋዜጠኞች የኦሮሞ ፀሐፊው የሆነውን ያሶ ካባባን ይዘው ወደ ጊንጪ ያመራሉ። እግረመንገድ ላይ የሚያገኟቸው ገበሬዎችም ሲጠይቋቸው በምስሉ ይታያል። እነዚያ በቀያቸው ማረፍያ እንኳን የሌላቸው ገበሬዎች የጋዜጠኞቹን መኪና ከብበው እንዲህ ሲሉ ይደመጣሉ። "መሬታችንን ቀምተው ለነጮች ሰጡብን። እኛንም በታተኑን ..."

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ግብር ለሚገባው ግብር ገብሩ”

ፕሮፌሠር ጌታቸው ኃይሌ

Prof. Getachew Hahile. ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ

የክርስቲያኖቹ መጽሐፍ “ግብር ለሚገባው (ሹም) ግብር ገብሩ” ይላል። ግብር ለማይገባው እንደወያኔ ላለ ገዢ ግን ግብር ስለማይገባው አንዲት ቀይ ቤሳ አታቅምሱት ማለቱ ነው። ጊዜ ስለሰጠው ቀምቶ ይወስዳል። ግን ብዕሬ ስቦኝ ነው እንጂ ለማለት የፈለግሁት እንኳን “አድናቆት ለሚገባቸው የኦሮምኛ ተናጋሪ የጎሣ ፖለቲከኞች አድናቆት ስጧቸው” ለማለት ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወንድም እህቶቻችን የት አሉ?

ግርማ ካሳ

በአጋዚ ጦር በአምቦ ከተማ የተገደለው የግርማ ረጋሳ ቤተሰቦች

ሁለት ወንድማማቾች ናቸው። ቃየን እና አቤል ይባላሉ። በዘፍጥረት ምዕራፍ 4 ላይ የተጻፈው ነው። “ቃየን አቤልን ና ወደ ሜዳ እንሂድ አለው። በሜዳም ሳሉ ቃየን በወንድሙ አቤል ላይ ተነሳበት። ገደለውም” ይለናል ቃሉ። ደም ፈሰሰ። የወንድም ደም በወንድም እጅ። እግዚአብሔር በሆነው ነገር አዘነ። ለቃየንም ጥያቄ አቀረበለት። “ወንድምህ አቤል ወዴት ነው?” አለው። ቃየንም መለስ “ እኔ የወንድሜ ጠባቂ ነኝን?” አለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እነ ሌንጮ በጎቹን ለተኩላዎች አሳልፈው መስጠት የለባቸውም

ናኦሚን በጋሻው

Lencho Leta. ኦቦ ሌንጮ ለታ

በኦሮሞ ዴሞክራቲክ ግንባር፣ ኦዴግ ውስጥ ያሉ አመራሮች በጣም የተከበሩ በሳል አመራሮች ናቸው። ለዓመታት በትግሉ ውስጥ ያለፉ፣ በርግጥም ለኦሮሞው ማኅበረሰብ የሚበጀውን እና የሚጠቅመውን የተረዱ። በኦሮሞውና በሌላው ማኅበረሰብ መካከል አለመተማመን እና መጠራጠር እንዳለ፣ ይሄንንም ለመግዛት እና ለመበዝበዝ እንዲያመቸው ሆን ብሎ ያደረገው ሕወሃት እንደሆነ በሚገባ የሚያውቁ። የኦሮሞው ማኅበረሰብ ከሌላው ጋር ያለውን ግንኙነትና ትስስር አጠናክሮ ለሁሉም እኩል የሆነች ኢትዮጵያን ለመገንባት ይቻል ዘንድ ፍላጎት አላቸው። በፖለቲካ አመለካከታቸው ጥሩ መስመር ላይ ያሉ ነው የሚመስሉት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጥያቄ ለአንባገነኖች፤ ዓለምን የሚገዛው ኃይል የቱ ነው?

ጓድ ካፍትሌ

ጥያቄ ለአንባገነኖች፤ ዓለምን የሚገዛው ኃይል የቱ ነው?

"Whoever wishes to foresee the future must consult the past; for human events ever resemble those of preceding times. This arises from the fact that they are produced by men who ever have been, and ever shall be, animated by the same passions, and thus they necessarily have the same results." Machiavelli

የዴሞክራሲ ጽንሰ ሀሳብ በዓለም ላይ ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት የተለያዩ የአስተዳደር ስልቶች ተግባራዊ ለማድረግ ተሞክሯል። አብዛኞቹ የአስተዳደር ስልቶች ግን ኃይልን መሠረት ያደረጉ ስለነበሩ በመሪና በተመሪዎች መካከል ከፍተኛ ቅራኔን ሲያሳድር ኖሯል።መሪዎቹ ለሚገዙት ሕዝባቸው ወፍራም ዱላ ካሳዩ ሕዝቡ ቀጥ ለጥ ብሎ ይገዛልኛል ብለው ስለገሚገምቱ የሥልጣን ዕድሜያቸውን ለማራዘም የሚሊዮኖችን ደም በከንቱ አፍስሰዋል። የአንድ ቀን የሥልጣን ዕድሜያቸውን በአንድ ሺህ ሰዎች ደም ያቆዪታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ይቅርታ” ወይም “ሰላም”

ተስፋዬ ገብረአብ

PM Halemariam Dessalegn daughter wedding. ጠ/ሚ ኃይለማርያም በቅርቡ ሴት ልጃቸውን የሞቀ ሠርግ ደግሰው ሲድሩ

ኃይለማርያም ደሳለኝ ባለፈው ሣምንት ያደረጉት ቃለመጠይቅ አነጋጋሪ ነበር። ከኦሮሞ ህዝብ አመጽ ጋር በተያያዘ የሰነበተውን ችግር ሌላ አካል ላይ ማላከክ እንደማይገባ መናገራቸው ከኢህአዴግ ጠባይ አንፃር ያልተለመደ ነበር። በውስጥ ባለ ችግር ምክንያት የህዝብ ጥያቄዎች ፈጣን ምላሽ ባለማግኘታቸው ህዝብና መንግሥት ተቃቅረው ጉዳዩ ወደ ግጭት ደረጃ መድረሱን ማመናቸው አንድ እርምጃ ወደፊት ነው። ችግሩ የመልካም አስተዳደር እጦት መሆኑን መግለፅ መቻላቸው ይደነቃል። ኃይለማርያም በዚህ ደረጃ ችግሩን አምነውና ተቀብለው ሲያበቁ፤ በመጨረሻ ለተፈጠረው ችግር በጥቅሉ ህዝብን ይቅርታ ጠይቀዋል። ይቅርታ ጥየቃው ካንገት በላይ ነው ወይስ ካንገት በታች ለጊዜው ባናውቅም፤ ይቅርታ መጠየቅ በራሱ ሥልጣኔ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ሪፖርት መድረሻው

ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ PM Hailemariam Desalegnግርማ ሠይፉ ማሩ

“የመልካም አስተዳደር ችግር እንፈታለን፤ ሥልጣን ግን አንለቅም” መሆኑ ነው?
የጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ሪፖርትን በወፍ በረር ስንቃኛው የሚከተለው ይዘት እንዳለው መረዳት እንችላለን። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዓመቱ ከመጠናቀቁ ቀደም ብለው የዕድገት ቅናሽ እንደሚኖር በሰበብ ደግፈው አምነዋል። ይህም ደግሞ ገዢው ፓርቲ ከአስራ አንድ በመቶ የእድገት ልክፍት በግድም ቢሆን መላቀቁን የሚያሳይ ነው። ከዚህ ቀደም የፈለገውን ያህል ተግዳሮት ቢፈጠር ያልተተገበሩ ግዙፍ ዕቅዶች ዝርዝር ቢቀርብም “ቢሆንም 11 ከመቶ አድገናል” እንደ ነበር አንዘነጋውም። ጠቅላይ ሚኒሰትሩ የእድገት ቅናሽ መኖሩን ቢያምኑም “ትንሽ ቅናሽ ያሳያል” በሚል ማለፋቸው ዝናብ ከዘነበ መልሶ ለማቅራራት ዝግጅት እንዳለ አመላካች ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ