ባለ ሐይኩ ሲጠየቅ
ሰሞኑን BETSY AND THE SUPERCOPTER በሚል ርእስ አዲስ መጽሐፍ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ለኅትመት በቅቷል። ደራሲው ዓለማየሁ ታዬ ከዚህ ቀደም ባሳተማቸውና “የዓለማየሁ ሩባያት”፤ “ግራፊቲ” እና “ሐይኩ” በተሰኙ የግጥም መድበል መጽሐፎች እንዲሁም “ጣፋጭ ተረቶች” በሚል ርእስ ባሳተመው ትርጉም የህጻናት መጽሐፍ እናውቀዋለን። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲና በህንድ ፑኔ ዩኒቨርስቲ በሥነጽሁፍና ሳይኮሎጂ አሁንም በአሜሪካ የተለያዩ ኮሌጆች ትምህርቱን በመከታተል ላይ የሚገኘው ዓለማየሁ ታዬ ኢትዮጵያ ውስጥ በሬዲዮና በኅትመት ጋዜጠኝነት ሰርቷል። በአሁኑ ወቅት በሎስ አንጀለስ ከተማ ቪሌጅ ግሌን ዌስት በተሰኘ ትምህርት ቤት በረዳት አስተማሪነት /Teacher’s Aide/ በመስራት ላይ ይገኛል። የአዲሲቱ መጽሐፍ ለኅትመት መብቃት ምክንያት ሆኖት ታሪኩ ኃይሉ በገጣሚው ስራዎች ላይ ከገጣሚው ጋር ያደረገውን ሰፋ ያለ ቃለምልልስ እነሆ!
ሙሉውን አስነብበኝ ...