ለወ/ሮ አረጋሽ አዳነ አሥራ አራት ሺህ ብር ተሰበሰበ

W/ro Aregash Adane ወ/ሮ አረጋሽ አዳነEthiopia Zare (እሁድ መጋቢት 26 ቀን 2002 ዓ.ም. April 4, 2010)፦ የቀድሞ የህወሓት ታጋይና በአሁኑ ሰዓት ዓረና-መድረክን በመወከል አቶ መለስ ዜናዊን በአድዋ በመፎካከር ለመጣል ቆርጠው ለተነሱት ወ/ሮ አረጋሽ አዳነ በቫንኩቨርና አካባቢዋ ነዋሪዎች የተዘጋጀው የገንዘብ ማሰባሰብ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን አዘጋጆቹ ገለጹ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

በፋሲካ በዓል የገበያው ዋጋ ንረት ታይቷል ተባለ

ዶሮ 80 ብር፣ ፍየል እስከ 2250 ብር፣ እንቁላል 2 ብር ተሽጧል

Ethiopia Zare (እሁድ መጋቢት 26 ቀን 2002 ዓ.ም. April 4, 2010)፦ በዓለ ትንሣዔ በመላው ኢትዮጵያ የሚከበር እንደመሆኑ እንደባለፉት በዓላት ሁሉ ዘንድሮም የገበያ ዋጋ ንረት የታየበት እንደነበር ተገለጸ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

መድረክ በአዲስ አበባ አራት ህዝባዊ ስብሰባዎችን አደረገ

“የኢህአዲግ ደጋፊዎች ሳይቀሩ “ብርቱካን ትፈታ” ብለው መጮህ አለባቸው” አቶ ስየ አብርሃ

Ethiopia Zare (ሰኞ መጋቢት 20 ቀን 2002 ዓ.ም. March 29, 2010)፦ መጋቢት 18 እና 19 ቀን በ4 የተለያዩ ሥፍራዎች የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎች ጥምረት የሆነው መድረክ፤ በአዲስ አበባ ከተማ ህዝባዊ ስብሰባ አካሂዷል። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የተስፋዬ ገብረአብ አዲስ መጽሐፍ ገበያ ላይ ሊውል ነው

Yedrasiw Mastawesha / የደራሲው ማስታወሻአዲሱ መጽሐፍ “የደራሲው ማስታወሻ” የተሰኘ ሲሆን፣ ቀጣዩ ደግሞ “የስደተኛው ማስታወሻ” ነው

Ethiopia Zare (እሁድ መጋቢት 19 ቀን 2002 ዓ.ም. March 28, 2010)፦ የደራሲና ጋዜጠኛ ተስፋዬ ገብረአብ “የደራሲው ማስታወሻ” የተሰኘው አዲሱ መጽሐፍ የፊታችን ሚያዝያ 2 ቀን 2002 ዓ.ም. (አፕሪል 10 ቀን 2010 እ.ኤ.አ.) በገበያ ላይ እንደሚውል የመጽሐፉ አሳታሚ “ነፃነት አሣታሚና አከፋፋይ” ለኢትዮጵያ ዛሬ በላከው መልዕክት ገለጸ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

በቫንኩቨር ለወ/ሮ አረጋሽ አዳነ ገንዘብ ሊሰበሰብ ነው

W/ro Aregash Adane, ወ/ሮ አረጋሽ አዳነን ‘አድዋ ለአረጋሽ፣ አረጋሽ ለአድዋ’ የስብሰባው መሪ መፈክር

Ethiopia Zare (ቅዳሜ መጋቢት 18 ቀን 2002 ዓ.ም. March 27, 2010)፦ በመጪው ምርጫ በትግራይ ክልል ውስጥ በአድዋ ከተማ የአቶ መለስ ዜናዊ ተፎካካሪ ሆነው የሚቀርቡት ወ/ሮ አረጋሽ አዳነን ለማበረታታትና በምርጫው እንዲያሸንፉ ለማገዝ በቫንኩቨር (ካናዳ) ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አዘጋጆቹ ለኢትዮጵያ ዛሬ ገለጹ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

አድማ በታኝ ኃይል በጃንሜዳ ልምምድ እያደረገ ነው

የወ/ት ብርቱካን ቀበሌ በ300 ፌደራሎች ይጠበቃል

Ethiopia Zare (ቅዳሜ መጋቢት 18 ቀን 2002 ዓ.ም. March 27, 2010)፦ የፌደራሉ መንግሥት አድማ በታኝ የፖሊስ ኃይል አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በተለያዩ ሥፍራዎች ተደጋገሚና ያልተቋረጠ “የአድማ ብተና” ሥልጠናዎችን እያካሄደ ነው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

“የአንድነት መንፈሥ ያላቸው ኢትዮጵያና ኤርትራ መዋሃድ አለባቸው” ኮ/ል አምሳሉ ገብረዝጊ ገብሩ

Ethiopia Zare (ዓርብ መጋቢት 17 ቀን 2002 ዓ.ም. March 26, 2010)፦ በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል ዳግማዊ የህዝብ ውህደትና አንድነት ለማምጣት መንግሥትን መጠበቅ አያስፈልግም ተባለ። ይህን ያሉት በጥር ወር 11ኛ ቀን 2002 ዓ.ም. “የኤርትራ መዘዝ” የተሰኘ መጽሐፋቸውን ለአንባቢያን ያደረሱት፣ ኮሎኔል አምሳሉ ገብረዝጊ ገብሩ የተባሉት የቀድሞ የኢትዮጵያ ሠራዊት አዛዥ ናቸው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ አንዷለም አራጌ “ቪዛ’ ተከለከለ

Ethiopia Zare (ረቡዕ መጋቢት 15 ቀን 2002 ዓ.ም. March 24, 2010)፦ የአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ዋና ፀሐፊ አቶ አንዷለም አራጌ “ጠንካራ ህዝባዊ ድጋፍ ሊያገኝ ይችላል” ከሚባሉት ፓርቲዎች አንዱ የሆነውን መድረክን በመወከል በቅርቡ ከአዲስ አበባ ወደ ዋሽንግተን ዲሲ ያቀናል የተባለው የልዑካን ቡድን አባል ሆነው ቢመረጡም፤ የመውጫ ፈቃድ (ቪዛ) መከልከ ተገለጸ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

መድረክ በአዲስ አበባ ከህዝብ ጋር ተወያየ

“የአቶ መለስን ጤንነት እንድንጠራጠረው ከማድረጉ ውጪ የተለየ ነገር የለውም” ዶ/ር ነጋሶ

“ስለወ/ት ብርቱካንም በግልጽ እንዳንናገር በይፋ ሲያስጠነቅቁንም ነበር” አቶ አንዷለም አራጌ

Ethiopia Zare (ሰኞ መጋቢት 13 ቀን 2002 ዓ.ም. March 22, 2010)፦ እሁድ መጋቢት 12 ቀን 2002 ዓ.ም. መድረክ ኃይሌ ገብረሥላሴ ጎዳና በሚገኘው የውሃ ልማት መ/ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ከህዝብ ጋር ተወያይቷል። ሁለት ወር የቀረውን የ2002 ምርጫ በተመለከተ መድረክ ህዝቡን በመዲናይቱ ሲጠራ የዕለተ እሁዱ ለአራተኛ ጊዜ ነው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፕ/ት ኦባማ የህዝባቸውን የሕክምና መብት አስከበሩ

Presidant Barack Obamaረቂቅ የሕክምና ሕጉ በሰባት ድምፅ ልዩነት ፀደቀ

Ethiopia Zare (ሰኞ መጋቢት 13 ቀን 2002 ዓ.ም. March 22, 2010)፦ ዩናትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ ዜጎች የሕክምና መብታቸው የተከበረባት ሀገር ልትሆን ነው። የዚህ ታሪካዊ ውጤት ባለቤት የመጀመሪያው ጥቁር አሜሪካዊ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ ናቸው። ሙሉውን አስነብበኝ ...