በእነ ጃዋር መሐመድ ላይ በግልጽ ችሎት ሊሰማ የነበረው የዓቃቤ ሕግ ምስክሮች ቃል እንዳይሰማ ታገደ

Jawar Mohammed (L), Bekele Gerba (R)

አቶ በቀለ ገርባ የኮቪድ 19 ክትባት እንዲሰጣቸው ጠየቁ

ኢዛ (ማክሰኞ ሚያዝያ ፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 13, 2021)፦ ባሳለፈው ሳምንት በእነ ጃዋር መሐመድ ላይ በዝግ ችሎት የምስክሮቼን ላሰማ የሚል ጥያቄው ውድቅ የተደረገበት ዓቃቤ ሕግ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ በማለቱ፤ ከዛሬ ማክሰኞ ሚያዝያ 5 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ በግልጽ ችሎት ሊሰማ የነበረው የጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ምስክሮች ቃል እንዳይሰማ አሳገደ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መከላከያ በሕወሓት ቡድን ታጣቂዎች ላይ እርምጃ ወሰደ

ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ

የሕወሓት አመራርና አባላት ከአገር ሊወጡ ሲሉ በቁጥጥር ሥር ውለዋል

ኢዛ (ማክሰኞ ሚያዝያ ፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 13, 2021)፦ በትግራይ ክልል በስምንት የተለያዩ አካባቢዎች ሲንቀሳቀስ የነበረ የሕወሓት የሽፍታ ቡድን በአገር መከላከያ ሠራዊት እርምጃ እንደተወሰደበት ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የምሥራቅ አፍሪካ አገሮች ከፍተኛ የፖሊስ መኮንኖች አዲስ አበባ ላይ እየሠለጠኑ ነው

Ethiopian Police University

ኢትዮጵያን ጨምሮ ከኡጋንዳ፣ ከኮሞሮስ፣ ከጅቡቲ፣ ከሶማሊያ፣ ከኬንያ እና ከብሩንዲ የተውጣጡ ናቸው

ኢዛ (ሰኞ ሚያዝያ ፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 12, 2021)፦ የምሥራቅ አፍሪካ ተጠባባቂ ኃይል አባል አገራት ከፍተኛ የፖሊስ መኮንኖች በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሥልጠና እየተሰጠ መኾኑን የምሥራቅ አፍሪካ ተጠባባቂ ኃይል አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የነዳጅ እጥረትና አገሪቱን እያጐበጠ ያለው የነዳጅ ወጪ

በአገሪቱ ከሚገኙት ነዳጅ ማደያዎች አንዱ

የእጥረቱ መንሥኤ በሶማሌና በአፋር ክልሎች አዋሳኝ በተፈጠረ ግጭት ነዳጅ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች እንደልብ መንቀሳቀስ አለመቻላቸው እና ከሱዳን የሚገባው ነዳጅ በአግባቡ እየገባ ባለመኾኑ ነው የሚሉ አሉ

ኢዛ (እሁድ ሚያዝያ ፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 11, 2021)፦ ባለፉት ሁለት ቀናት በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች የተፈጠረው የነዳጅ እጥረት ተገልጋዮችን ሲያጉላላ በተለይ አዲስ አበባ ከተማ በትራፊክ መጨናነቅ ምክንያት ኾኖ ታይቷል። ዛሬን ጨምሮ ባለፉት ሦስት ቀናት በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ አብዛኞቹ ነዳጅ ማደያዎች ነዳጅ የለንም በሚል አገልግሎት እየሰጡ አልነበረም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፌስቡክ በህዳሴ ግድብ ላይ ያነጣጠሩ መልእክቶችን ከግብጽ ሲያሠራጩ የነበሩ አካውንቶችን ዘጋ

Facebook

17 የፌስቡክ አካውንቶች፣ 6 ገጾች እና 3 የኢንስታግራም አካውንቶችን መዝጋቱን ገልጿል

ኢዛ (ሐሙስ መጋቢት ፴ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 8, 2021)፦ ኢትዮጵያን ጨምሮ ሱዳን እና ቱርክን ዒላማ አድርገው መረጃ ሲያሠራጩ ነበር የተባሉ እና መቀመጫቸውን ግብጽ ላይ ያደረጉ የማኅበራዊ ሚዲያ አካውንቶችን እንደዘጋ ፌስቡክ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በ1147 አመራር እና አባላት ላይ እርምጃ መውሰዱ ተገለጸ

Commissioner Getu Argaw

በምርጫው የጸጥታ ችግሮች እንዳይከሰቱ በልዩ ትኩረት እየሠራ እንደሚገኝ አስታወቀ

ኢዛ (ሐሙስ መጋቢት ፴ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 8, 2021)፦ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፤ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 1,147 የሚኾኑ የፖሊስ አመራር እና አባላት ላይ ቀላል እና ከባድ የዲሲፕሊን እርምጃ መውሰዱ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኦሮሚያ ክልል ኦነግ ሸኔን በ15 ቀን እደመስሳለሁ አለ

Getachew Balcha

ኦነግ ሸኔን ከመደምሰስ ባሻገር ከዘመቻው ጋር ያልተባበሩ እና ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ያልተወጡ የመንግሥት አመራሮችም ከመጠየቅ አያመልጡም ተብሏል

ኢዛ (ረቡዕ መጋቢት ፳፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 7, 2021)፦ ዛሬ ረቡዕ መጋቢት 29 ቀን 2013 ዓ.ም. ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የተሰማው አንድ መረጃ በብርቱ የሚጠበቅ፤ ምናልባትም አገሪቱን በአሁኑ ሰዓት ያለችበትን ያለመረጋጋትና ዘር ተኮር ጭፍጨፋን ያስቀራል ተብሎ የተገመተ ነው። ይህ ከክልሉ መንግሥት የተሰማው ዜና በአሁኑ ወቅት በጅምላ ጭፍጨፋ ቀዳሚ ተጠያቂ የኾነውን የኦነግ ሸኔ በአሥራ አምስት ቀን ውስጥ ልክ አስገባዋለሁ ማለቱ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በዝግ ችሎት ይሰማ የተባለው ምስክርነት ውድቅ ኾነ

Jawar Mohammed (L), Bekele Gerba (R)

በእነ አቶ ጃዋር ላይ የዓቃቤ ሕግ ምስክሮች በግልጽ ችሎት ምስክርነታቸው ይሰማ ተብሎ ብይን ተሰጠ

ኢዛ (ማክሰኞ መጋቢት ፳፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 6, 2021)፦ ዓቃቤ ሕግ በእነ ጃዋር መሐመድ ላይ በዝግ ችሎት ላሰማ ያለው የምስክር የአሰማም ሒደት ጥያቄ ውድቅ በማድረግ፤ ምስክሮቹ በግልጽ ችሎት ምስክርነታቸውን እንዲሰጡ ብይን ተሰጠ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ በኮቪድ 19 ጽኑ ሕሙማን ቁጥር የመጀመሪያውን ደረጃ ይዛለች

ዶ/ር ሚዛን ኪሮስ

ቫይረሱ በአሁኑ ጊዜ ባለባቸው ሰዎች ቁጥር ከአፍሪካ ቀዳሚ ናት

ኢዛ (ማክሰኞ መጋቢት ፳፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 6, 2021)፦ በኢትዮጵያ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ አሳሳቢ በሚባልበት በዚህ ሰዓት፤ በጽኑ ሕሙማን ቁጥር ከአፍሪካ የመጀመሪያውን ደረጃ ልትይዝ መቻሏ ተገለጸ። በአሁኑ ሰዓት ኮሮና ቫይረስ ባለባቸው ሰዎች ቁጥርም፤ ከአፍሪካ ቀዳሚነቱን እንደያዘች ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የብሮድካስት ባለሥልጣን አዳዲስ ዋናና ምክትል ዳይሬክተሮች ተሾሙ

Yonatan Tesfaye

አንዱ ተሿሚ ዮናታን ተስፋዬ ነው

ኢዛ (ሰኞ መጋቢት ፳፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 5, 2021)፦ በቅርቡ ኃላፊነታቸውን በገዛ ፍቃዳቸው በለቀቁት በቀድሞ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ምትክ እና በሹመት ወደ ሌላ መሥሪያ ቤት በሔዱት ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች ምትክ አዳዲስ ኃላፊዎች ተሾሙ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ