ለአለቃ አያሌው ታምሩ መታሰቢያ ድረ ገጽ ተከፈተ

Aleqa Ayalew TamiruEthiopia Zare (ኀሙስ ነኀሴ 8 ቀን 2000 ዓ.ም. August 14, 2008)፦ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሊቃውንት ጉባዔ ዋና ሰብሳቢ ለነበሩት ለአለቃ አያሌው ታምሩ መታሰቢያ ይሆን ዘንድ በማሰብና ሥራዎቻቸውን ለምዕመናን ለማቅረብ ሲባል በስማቸው ድረ ገጽ መከፈቱን ልጃቸው ወ/ሮ ጽዮን አያሌው ለኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ ገለጸች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንድነት ከምርጫ ቦርድ ምላሽ ተሰጠው

ቦርዱ የላከው ደብዳቤ ”ለአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ (አንድነት) ፓርቲ” በሚል ነው

Ethiopia Zare (ሰኞ ነኀሴ 5 ቀን 2000 ዓ.ም. August 11, 2008)፦ ”አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ”ን በምርጫ ቦርድ ለማስመዝገብና ሕጋዊ ፈቃድ ለማግኘት ለቦርዱ ማመልከቻ ያስገቡት የቀድሞው የቅንጅት አመራሮች ጥቂት ማስተካከያዎችን እንዲያሟሉ በድጋሚ ከምርጫ ቦርድ በደብዳቤ ተገለጸላቸው። ደብዳቤው የተፃፈው ”ለአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ (አንድነት) ፓርቲ” በሚል መሆኑን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለወጪ ቁጠባ ኢትዮጵያውን አትሌቶች በቤጂንጉ መክፈቻ አልተሳተፉም

Beijing Olympics 2008ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የሚሳተፉበትን የጊዜ ሠሌዳና ስለኦሎምፒኩ መረጃዎች ይዘናል

Ethiopia Zare (እሁድ ነኀሴ 4 ቀን 2000 ዓ.ም. August 10, 2008)፦ ዓርብ ነኀሴ 2 ቀን 2000 ዓ.ም. (በፈረንጆች 080808) በቻይና ቤጂንግ ኦሎምፒክ የመክፈቻ ስነሥርዓት ላይ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ያልተገኙ ሲሆን፣ የተገኙት አብዛኞቹ የኢህአዴግ ሰዎች መሆናቸውን ለመረዳት ችለናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በቡታጅራ በወረዳ ስያሜ በተነሳ ብጥብጥ አራት ሰዎች ቆሰሉ

Ethiopia Zare (እሁድ ነኀሴ 4 ቀን 2000 ዓ.ም. August 10, 2008)፦ በደቡብ ክልል በቡታጅራ ከተማ በጉራጌ ዞን በሚገኙ ሁለት ወረዳዎች ስያሜ አሰጣጣጥ ጋር በተያያዘ በነዋሪዎችና በፖሊስ መካከል በተነሳ ግጭት አራት ሰው ሲቆስሉ፣ 12 ሰዎች መታሰራቸው ታስረዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ለረሃብተኛው ተጨማሪ ዕርዳታ ያስፈልገናል” የመንግሥት ባለሥልጣናት

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ነኀሴ 3 ቀን 2000 ዓ.ም. August 09, 2008)፦ ሐሙስ ዕለት የግብርናና ገጠር ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር አበራ ደሬሣ እና የአደጋና መከላከል ዝግጁነት ኤጀንሲ ዳይሬክተር ስምኦን መቻሌ ለዓለም አቀፍ የሚዲያ ሰዎች በሰጡት መግለጫ የረሃብተኛው ቁጥር መጨመሩንና አስቸኳዋይ የምግብ ዕርዳታ እንደሚስፈልግም ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንድ የኢህአዲግ የፓርላማ አባል እንግሊዝ አገር ጥገኝነት ጠየቀ

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ነኀሴ 3 ቀን 2000 ዓ.ም. August 09, 2008)፦ አቶ በለጠ ኢታና የተባሉ የገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ የፓርላማ አባል እና በፓርላማው የመንግሥት አስተዳዳር ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ፕሬዝዳንት በእንግሊዝ አገር ጥገኝነት መጠየቁ ታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሀገረማርያም በተነሳ የጎሣ ግጭት 8 ሰዎች ሞቱ

 

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ነኀሴ 3 ቀን 2000 ዓ.ም. August 09, 2008)፦ በግጦሽ መሬትና በድንበር ግጭት ምክንያት በተነሳ አለመግባባት በኦሮሚያ ክልል በቦረና ዞን በደቡብ ክልል የሚዋሰኑ ከአዲስ አበባ 534 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከምትገኘው ሀገረማርያም ከተማ 47 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኙ ሁለት ጎሣዎች መካከል በተነሳ ግጭት ስምንት ሰዎች መሞታቸውን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች አረጋገጡ።

 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የቴዲ አፍሮ ጠበቃ ተፈታ፣ ቴዲ ከጨለማ ቤት ወጣ

Ethiopia Zare (ዓርብ ነኀሴ 2 ቀን 2000 ዓ.ም. August 08, 2008)፦ የቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ጠበቃ አቶ ሚሊዮን አሰፋ ባለፈው ረቡዕ ሐምሌ 30 ቀን 2000 ዓ.ም. ”ችሎት በመዳፈር” በሚል ለአንድ ወር ከሃያ ቀናት ከተፈረደበት በኋላ በጠቃው አቶ አበባ አሳምን አማካኝነት ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ተዘዋዋሪ ችሎት ይግባኝ በማለቱ አቶ ሚሊዮን ዛሬ ማምሻውን መፈታቱን እንዲሁም ቴዲ አፍሮ ደግሞ 27 ቀናት ታስሮ ከነበረበት ጨለማ ቤት እንዲወጣ መደረጉን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከ34 ዓመት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ስለድርቅ ተዘፈነ

Ethiopia Zare (ኀሙስ ነኀሴ 1 ቀን 2000 ዓ.ም. August 07, 2008)፦ ወጣት ሔኖክ ገብሬ ከኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ በጋራ በመተባበር ”ምንድንነው ምስጢሩ?” በሚል ርዕስ በሀገራችን በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያለውን ድርቅና ረሃብ በሚመለከት ነጠላ ዜማ በዛሬው ዕለት ለህዝብ አቅርቧል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...