አንድነት ስብሰባ ለማካሄድ ችግር እንደገጠመው ገለጸ

Letter to UDJ from City Government of Addis Ababa Ethiopia Zare (ቅዳሜ ግንቦት 15 ቀን 2001 ዓ.ም. May 23, 2009)፦ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ህዝባዊ ስብሰባዎችን ለማካሄድ በተደጋጋሚ ቢሞክርም የስብሰባ አዳራሽ አከራዮች ከአዲስ አበባ መስተዳደር ፈቃድ እንዲያመጡ እንደሚጠይቋቸውና ፓርቲው የህዝባዊ ስብሰባውን በመስቀል አደባባይ እንዲያደርግ መገደዱን የድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር ኢንጅነር ግዛቸው በተለይ ለኢትዮጵያ ዛሬ ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ ተመስገን ዘውዴ በፀና ታመዋል

Ato Temesgen Zewde አቶ ተመስገን ዘውዴውጭ ሀገር ሕክምና ካላገኙ ሕይወታቸው አስጊ ደረጃ ላይ ነው

Ethiopia Zare (አርብ ግንቦት 14 ቀን 2001 ዓ.ም. May 22, 2009)፦ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት እና በቅንጅት ስም ፖርላማ ገብተው አቋማቸውን በመግለጽ የህዝብን ድጋፍ ያገኙት አቶ ተመስገን ዘውዴ በጽኑ መታመማቸውንና ለከፍተኛ የሕክምና ዕርዳታ ወደ ውጭ መውጣት እንደሚኖርባቸው ሐኪሞች መወሰናቸውን የኢትዮጰያ ዛሬ ምንጮች አረጋገጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ አበባ እና አስመራ በመቋዲሾ ጉዳይ ተካረዋል

Ethiopia Zare (አርብ ግንቦት 14 ቀን 2001 ዓ.ም. May 22, 2009)፦ በሶማሊያ የአልሻባብ እና የሂዝቡ እስላም ተዋጊዎች፣ በሌላ መጠሪያ ስማቸው “የሶማሊያ ዳግማዊ ነፃነት ኃይል” ተፋላሚዎች፤ መቋዲሾን ዋነኛ ዒላማቸው አድርገው በመዋጋት ላይ ሲሆኑ አስመራንና አዲስ አበባ በሱማሊያ ጉዳይ በስተጀርባ መወነጃጀል መቀጠላቸው ተዘገበ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንድነት ችግሮቹን በውይይት መፍታቱን ገለጸ

Ethiopia Zare (ረቡዕ ግንቦት 12 ቀን 2001 ዓ.ም. May 20, 2009)፦ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ባለፉት ጊዜያት በማዕከላዊ ምክር ቤት አባላት ለድርጅቱና ለህዝብ ይፋ በሆነው ሰነድ ላይ በመነሳት ለሁለት ቀናት ስብሰባ በማካሄድ እልባት ላይ መድረሱን የድርጀቱ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊና ምክትል ሊቀመንበር ዶ/ር ኃይሉ አርኣያ በተለይ ለኢትዮጵያ ዛሬ ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አጨቃጫቂው የመያዶች ሕግ ታገደ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ግንቦት 11 ቀን 2001 ዓ.ም. May 19, 2009)፦ ከአንድ ዓመት በፊት ተረቅቆ መንግሥታዊ ባልሆኑ ድርጅቶችና በተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ውግዘት የደረሰበትና ሲያጨቃጭቅ የቆየው የበጐ አድራጐት ድርጅቶች እና ማኅበራት ሕግ በፓርላማ ፀድቆ በነጋሪት ጋዜጣ ከታተመ በኋላ ሰሞኑን ታግዶ በቀድሞው ሕግ ምዝገባ እንዲካሄድ መደረጉ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ግንቦት 7 ንቅናቄ በስዊድን ከኢትዮጵያውያን ጋር ውይይት አደረገ

Ato Chekol & Dr. Berhanu (080621 Stockholm)By Yonatan Tsegaye

Ethiopia Zare (ሰኞ ግንቦት 10 ቀን 2001 ዓ.ም. May 18, 2009)፦ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የሚመሩት ”ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ” በተለያዩ የአውሮፓ ከተሞች እየተዘዋወረ ህዝባዊ ስብሰባ እያካሄደ ሲሆን፣ የመጀመሪያውን ህዝባዊ ውይይት ባለፈው ቅዳሜ ግንቦት 8 ቀን 2001 ዓ.ም. ከሰዓት በኋላ በርካታ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት አደረገ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በዩሮቪዥን 2009 ኖርዌይ አሸነፈች

የአልባኒያዊቷ ተወዳዳሪ ስሟ ኢትዮጵያዊ ነው፣ ‘ኬይሲ ቶላ” ትባላለች

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ግንቦት 8 ቀን 2001 ዓ.ም. May 16, 2009)፦ ዛሬ ማምሻውን በተጠናቀቀው “ዮሮቪዥን” በመባል በሚታወቀውና በሞስኮ በተካሄደው 54ኛው የአውሮፓ ሀገሮች የሙዚቃ ውድድር ኖርዌይ አሸናፊ ሆነች። “ፌሪቴይልስ” በተሰኘው ዘፈኑ ኖርዌይን አሸናፊ እንድትሆን ያደረጋት የ23 ዓመቱ አሌክሳንደር ሪባክ የተሰኘው ድምፃዊ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመብራት መቋረጥ ችግር መፍትሔ አልተበጀለትም

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ግንቦት 8 ቀን 2001 ዓ.ም. May 16, 2009)፦ በአዲስ አበባ ከተማ በአንዳንድ አካባቢዎች በሣምንት ከሦስትና ከአራት ቀናት በላይ የመብራት መቋረጥና ካናካቴውም የመጥፋት ችግር እያጋጠመ መሆኑንና ችግሩ ካለፈው ሣምንት ረቡዕ ሚያዝያ 21 ቀን 2001 ዓ.ም. ወዲህ ባለው ጊዜ ተባብሶ መቀጠሉ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዓለም አቀፉ ሰልፍ በስዊድን በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ

By Matias Ketema

May 15, 2009 World wide rally, Sweden, Stockholm
 

Ethiopia Zare (ዓርብ ግንቦት 7 ቀን 2001 ዓ.ም. May 15, 2009)፦ ዛሬ በዓለም አቀፍ ደረጃ በስምንት ከተሞች የአሜሪካን መንግሥት በጠ/ሚ መለስ ዜናዊ መንግሥት ላይ ጫና እንዲያደርግ የተጠራ ዓለም አቀፍ ሰልፍ ተካሂዷል። በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም ሰልፈኛውን ለመቀላቀል ከከተማዋ እንብርት ብዙም ሳይርቅ ከሚገኘው የአሜሪካን ኤምባሲ የደረስኩት ሰልፉ በተጠራበት 14፡00 ሰዓት (በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር 8 ሰዓት) ላይ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...