ሰኔ አንድ ቀን የዲሞክራሲ ሰማዕታት ቀን ታስቦ ዋለ

አንድነት ‘ፅናት’ መጽሔትን አስመረቀ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሰኔ 2 ቀን 2001 ዓ.ም. June 9, 2009)፦ ሰኔ አንድ ቀን 2001 ዓ.ም. የዲሞክራሲ ሰማዕታት ቀን በማለት አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በዋና ጽሕፈት ቤቱ ቅጥር ግቢ ከምርጫ 97 በኋላ በግፈኛው የአጋዚ ጦር የተጨፈጨፉትን ሰማዕታት አስቦ መዋሉን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ዘገቡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመብራት ስርጭት እጥረት ተባብሷል

አጥጋቢ ዝናብ ካልኖረ በኢትዮጵያ ያለው ችግር እንደሚባባስ ተገለጸ

Ethiopia Zare (ሰኞ ሰኔ 1 ቀን 2001 ዓ.ም. June 8, 2009)፦ የመብራት ስርጭት እጥረት በመላ ሀገሪቱ ከዕለት ወደ ዕለት እየተባባሰ መምጣቱንና ብዙ ቦታዎች በሁለት ቀን አንድ ቀን ብቻ እየደረሳቸው ከመምጣቱም በላይ ከመብራት ጋር የተያያዙ ዕቃዎችን የኤሌክትሪክ ውጤቶች ዋጋ በእጥፍ እየጨመረ መሆኑን ከአዲስ አበባ የደረሰን ዜና አስረዳ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ክብርት ካሪና ሄግ የኢትዮጵያውያን ስደተኞች ጉዳይ እንዳሳሰባቸው ገለጹ

ክብርት ካሪና ሄግ Carina Häggለኢሚግሬሽን ሚኒስትሩ ጥያቄ አቅርበዋል

Ethiopia Zare (ሐሙስ ግንቦት 27 ቀን 2001 ዓ.ም. June 4, 2009)፦ ለአውሮፓ ፓርላማ እየተወዳደሩ የሚገኙት የስዊድን ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ የፓርላማ አባል የሆኑት ክብርት ካሪና ሄግ ከስዊድን እንዲባረሩ የተወሰነባቸው የኢትዮጵያን ስደተኞች ጉዳይ እንዳስጨነቃቸውና እንዳሳሰባቸው ገልጸው፣ ለኢሚግሬሽን ሚኒስትሩ ቶቢያስ ቢልስተረም የስደተኞቹን ጉዳይ ትኩስ መረጃን መሠረት በማድረግ እንዲታይ ጥያቄ አቀረቡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፀረ-ሽብር ረቂቅ አዋጁ በዜጐች ላይ ሽብር እየፈጠረ ነው

Ethiopia Zare (ሐሙስ ግንቦት 27 ቀን 2001 ዓ.ም. June 4, 2009)፦ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸድቆ ለተወካዮች ምክር ቤት የተላከው የፀረ-ሽብር ረቂቅ አዋጅ የኢህአዲግ ደጋፊ ያልሆኑትን ነጥሎ የመምቻ የሕግ ሽፋን ይሆናል በሚል በዜጐች ላይ ሽብር እየፈጠረ መሆኑን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች አረጋገጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዓባይ ጦርነት “አይቀሬ ነው” ተባለ

ኢትዮጵያ ደህንነቷን የሚያስጠብቅ ህዝባዊ መንግሥት የላትም

Ethiopia Zare (ሐሙስ ግንቦት 27 ቀን 2001 ዓ.ም. June 4, 2009)፦ ጊዜው ቢረዝም እንጂ የዓባይ ጦርነት “አይቀሬ” መሆኑን የሕግና የታሪክ መምህር የሆኑት ኢትዮጵያዊ አቶ ፋሲል አምደፅዮን አስታወቁ። እኚህ ባለሙያ ከወደ አሜሪካ ሆነው የቴክሳስ ዩኒቨርሲቲ በሚያሳትመው የሕግ መጽሔት ላይ ዓባይን የተመለከተ ለንባብ ባበቁት ጥናታዊ ጽሑፋቸው፣ “የውሃ ጦርነት የዓባይን አጠቃቀም ተከትሎ በምሥራቅ አፍሪቃ መቀስቀሱ የማይታበል እውነት መሆን ችሏል” ብለዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢንጂንየር ኃይሉ ሻውል በቃሌ ሲምፖዚየም ንግግር አደረጉ

ኢንጂንየር ኃይሉ ሻውል Eng. Hailu Shawel‘ግንቦት 20 ቀን የታሪክ አጋጣሚ ምጸት ሆኖ አልፏል’ ዶ/ር ኃይሉ አርኣያ

Ethiopia Zare (ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2001 ዓ.ም. June 1, 2009)፦ ግንቦት 20 ቀን ለኢህአዲግ ሥልጣኑን የተቆጣጠረበት 18ኛ ዓመት የድል ቀን ሲሆን፣ ለእኛ ደግሞ ዲሞክራሲ የተረገጠበትና መሪያችን ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ወደ እስር የተጣለችበት አምስተኛ ወር ነው ሲሉ ዶ/ር ኃይሉ አርኣያ በተለይ ለኢትዮጵያ ዛሬ ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአዲስ አበባ የቴሌ ኮሙኒኬሽን መስሪያ ቤት ተቃጠለ

ከፍተኛ ንብረት ወድሟል

Ethiopia Zare (እሁድ ግንቦት 23 ቀን 2001 ዓ.ም. May 31, 2009)፦ ዛሬ ጠዋት ከቀኑ አራት ሰዓት አካባቢ በተነሳ ቃጠሎ በአዲስ አበባ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጎን የሚገኘው ዋናው የቴሌ ኮሙኒኬሽን ኮርፖሬሽን ህንጻ በተነሳ ቃጠሎ ከፍተኛ ውድመት መድረሱን ምንጮቻችን ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አያት ኩባንያ 300 ሠራተኞቹን አሰናበተ

Ethiopia Zare (እሁድ ግንቦት 23 ቀን 2001 ዓ.ም. May 31, 2009)፦ በኢትዮጵያ ከተሞች በተለይም በአዲስ አበባ የጋራ መኖሪያ ቤቶችንና መንደሮችን በመገንባት እና እነዚህንም ቤቶችና መንደሮች በመሸጥ ተግባር የተሠማራው “አያት የመኖሪያ ቤቶችና መንደሮች ግንባታ አክሲዮን ኩባንያ”፤ ለዓመታት በቋሚና በኮንትራት ቀጥሮ ሲያሠራቸው የቆየውን ሠራተኞቹን ያሰናበተ መሆኑን አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የABC ንብረት ተወረሰ

ሦስት ሰዎች ታሰረዋል፤ ከግንቦት 7 ጋር ይጠረጠራል

Ethiopia Zare (እሁድ ግንቦት 23 ቀን 2001 ዓ.ም. May 31, 2009)፦ የአዲስ ብሮድካስቲንግ ኤጀንሲ ንብረት የነበረ የ7 ሚሊዮን ብር የራዲዮ ስቱዲዮ መሣሪያ ከትናንት በስቲያ በመንግሥት ኃይሎች ውርስ ተደረገ። ግንቦት 20 ማታ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በተሠራጨ ዜና ንብረቱ የተወረሰው “በሕገ ወጥ መንገድ የገባ በመሆኑ ነው” ተብሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

”የወያኔ መሪዎች የትግራይን ህዝብ አይወክሉም” ፕ/ት ኢሣያስ አፈወርቂ

ፕ/ት ኢሣያስ አፈወርቂ Presidant Isaias Afwerki70 ደቂቃ የፈጀውን የቲቪ ቃለምልልስ ይዘናል

Ethiopia Zare (ረቡዕ ግንቦት 19 ቀን 2001 ዓ.ም. May 27, 2009)፦ የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሣያስ አፈወርቂ ለስዊድን ቴሌቭዥን በሰጡት ቃለምልልስ፤ ”የወያኔ/ኢህአዲግን መሪዎች ጥቂቶችና የየትኛውም የኢትዮጵያ ህዝብ/ብሔር ውክልና የሌላቸው ናቸው። የትግራይ ህዝብንም አይወክሉም።” ብለዋል። በዚሁ ቃለምልልስ ላይ ሲ.አይ.ኤ.ን፣ አሜሪካንን፣ ስዊድንን እና ወያኔ/ኢህአዲግን ወንጅለዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...