ቴዲ አፍሮ ከተከሰሰበት የቅጂ መብት ክስ በነፃ ተሰናበተ

Teddy AfroEthiopia Zare (ማክሰኞ ግንቦት 4 ቀን 2001 ዓ.ም. May 12, 2009)፦ አቶ አዲስ ገብሩ የተባሉ ሠዓሊ፣ ሥዕሎቼ ያለ ፈቃዴ በሰለሜ ክሊፕ ውስጥ ተካተውብኛል በሚል ባቀረቡት አቤቱታ፣ በፌደራል ዓቃቤ ሕግ አማካኝነት በአርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁንና በኤሌክትራ ሙዚቃ ቤት ባለቤት ላይ የቀረበውን ክስ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተመልክቶ በነፃ ቢያሰናብተውም፤ በይግባኝ የቀረበለት ፍርድ ቤት እንዲከላከል ወስኖ፣ መዝገቡን ወደ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተመልሶ የነበረ ሲሆን፣ በዛሬው ዕለት (ማክሰኞ ግንቦት 4 ቀን 2001 ዓ.ም.) ሁለቱም ተከሳሶች በነፃ ተሰናበቱ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከግንቦት ሰባት ጋር በተያያዘ የታሰሩት ጉዳያቸው በዝግ ችሎት ታየ

ፖሊስ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ጠየቀባቸው

Ethiopia Zare (ሰኞ ግንቦት 3 ቀን 2001 ዓ.ም. May 11, 2009)፦ ከግንቦት ሰባት ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው ከታሰሩት 40 እስረኞች ውስጥ 36 የሚሆኑት በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ዛሬ ግንቦት 3 ቀን 2001 ዓ.ም. ቀርበው ጉዳያቸው በዝግ መታየቱን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዝክረ ክብርት ዶ/ር ስንዱ ገብሩ

Ethiopia Zare (ሰኞ ግንቦት 3 ቀን 2001 ዓ.ም. May 11, 2009)፦ የመጀመሪያዋ ሴት የፓርላማ ተመራጭ፣ የጦር አርበኛ፣ ፀሐፊ- ተውኔት፣ ደራሲ፣ የመጀመሪያዋ ሴት ዲፕሎማት የነበሩት እና ባለፈው ሚያዝያ 12 በ93 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩትን የክብርት የዶ/ር ስንዱ ገብሩን ማንነት የሚዘክር “ዝክረ - ስንዱ ገበሬ”፣ “እናከብሮታለን!” በሚል ዝግጅት ባለፈው አርብ በእቴጌ መነን ት/ቤት ተከናወነ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአሜሪካ ሰብዓዊ መብት ሪፖርት ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት ያቀረበው ውንጀላ - እየተወነጀለ ነው

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ግንቦት 1 ቀን 2001 ዓ.ም. May 9, 2009)፦ በኢትዮጵያ ውስጥ ፖለቲካዊ እስር፣ የመብት ጥሰት፣ በጋዜጠኞች ላይ ወከባና ግድያ እንደሚፈፀሙ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በ2008 ዓመታዊ ሪፖርቱ ገልጿል። መንግሥት ሪፖርቱን “ከእውነት የራቀ ነው” በሚል በዝርዝር በማየት የማስተባበያ ሪፖርት አዘጋጅቶ በቁጥጥሩ ስር በሚገኘው የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ዝግጅቶች አቅርቧል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ማረሚያ ቤቶች በወ/ት ብርቱካን መብት ላይ የተሰጠውን ውሳኔ እንዲፈፀም መጥሪያ ተላከለት

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ግንቦት 1 ቀን 2001 ዓ.ም. May 9, 2009)፦ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበር ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ሚያዝያ 7 ቀን 2001 ዓ.ም. የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፍትሐብሔር ችሎት እንደማንኛውም እስረኛ እንዲጉበኙ ያስተላለፈው ውሳኔ ሳይከበር 23 ቀናትን ያስቆጠረ ሲሆን፣ ጠበቃው አቶ ተስፋዬ ደረሰ ይህን በማስመልከት ለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ስምንተኛ ፍትሐብሔር ችሎት ውሳኔው ይፈፀም ሲሉ አቤት በማለታቸው፤ ተከሳሹ የፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ውሳኔውን ፈፅሞ እንዲቀርብና የማይፈፀምበት ምክንያት ካለም ቀርቦ እንዲያስረዳ መጥሪያ ተልኮለታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቴዲ አፍሮ ፍርድ ቤት ቀርቦ ነበር

Teddy Afroለግንቦት አራት ተቀጠረ

Ethiopia Zare (ዓርብ ሚያዝያ 30 ቀን 2001 ዓ.ም. May 8, 2009)፦ ታዋቂው አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ከተከሰሰበት ሰው ገጭቶ ማምለጥ በተጨማሪ “ሰለሜ” በተሰኘው ክሊፕ ላይ ያለፍቃዴ ስዕሌን ተጠቅሟል በሚል ለቀረበበት ክስ ትናንት ሐሙስ ሚያዝያ 29 ቀን 2001 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ቀርቦ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከግንቦት ሰባት ጋር በተያያዘ ክሳቸው በጦር ፍርድ ቤት የሚታይም አሉ

አቶ በረከት ከጋዜጠኞች ጋር ያደረጉትን ቃለምልልስ ይዘናል

Ethiopia Zare (ረቡዕ ሚያዝያ 28 ቀን 2001 ዓ.ም. May 6, 2009)፦ መንግሥት ከግንቦት ሰባት ጋር በተያያዘ ”የግድያና የሽብር ተግባር ሊፈጽሙ ሲሉ ያዝኳቸው” ያላቸውን በሥራ ላይ የነበሩና የተባረሩ ጄኔራሎችና የመከላከያ ሠራዊት አባላት ክሳቸው በመደበኛ ፍርድ ቤት ይታይ ወይስ በጦር ፍርድ ቤት የሚለውን ለመወሰን እየተወያየ መሆኑን የኢትዮጵያ ዛሬ ምጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የወዛደሮች ቀን በዓል በከፍተኛ ድምቀት ወ/ት ብርቱካንን በማሰብ ተከበረ

By Matias Ketema (Sweden)

የዓለም የሠራተኞች ቀን በስዊድን, Mayday in Sweden 2009

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ሚያዝያ 24 ቀን 2001 ዓ.ም. May 2, 2009)፦ በትናንትናው ዕለት የዓለም የወዛደሮች ቀን (ሜይዴይ) በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም በሾሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲና በሠራተኛው ማኅበር በተዘጋጀው የወዛደሮች ቀን በዓል ብዙ ሺህ ሰልፈኛ በተገኘበት ተከብሮ የዋለ ሲሆን፣ የስዊድን የሠራተኛ ማኅበር ሊቀመንበር ባንኛ ቬድን የወ/ት ብርቱካን እስር እንዳሳሰባቸው ባደረጉት ንግግር ላይ ገልፀዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...