የአንድነት ሠላማዊ ሰልፍ ተከለከለ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ መጋቢት 29 ቀን 2001 ዓ.ም. April 7, 2009)፦ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ከፍተኛ የፓርቲው አመራሮችና በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ ተጠሪዎችን በማካተት ወ/ት ብርቱካን የታሰረችበትን ሂደት በመቃወም የፊታችን ኀሙስ ሚያዝያ 1 ቀን 2001 ዓ.ም. (April 9, 2009) ጠርቶት ነበረው ሠላማዊ ሰልፍ በመንግሥት በኩል ፈቃድ በመከልከሉ በዕለቱ ሰልፉ እንደማይካሄድ ታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“መንግሥት በሰብዓዊ መብት ላይ አሳፋሪ ሪከርድ የለውም” ሲሉ አቶ በረከት ገለጹ

Ato Bereket SemeonEthiopia Zare (ማክሰኞ መጋቢት 29 ቀን 2001 ዓ.ም. April 7, 2009)፦ በሚንስትሩ አቶ በረከት ስምዖን የሚመራው የመንግሥት ጉዳዮች ኮምዩኒኬሽን ጽ/ቤት በሣምንት ውስጥ በመንግሥት የሚከናወኑ ታላቅቅ ጉዳዮች ላይ ለመንግሥት፣ ለግልና ለውጭ ሚዲያዎች በየሣምንቱ መግለጫ ለመስጠት መወሰኑን አስታወቀ። በዚህም መሰረት በሣምንቱ የተከናወኑና የሚከናወኑ ተግባራት ናቸው ባላቸው ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጥቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአንድነት ፓርቲ አመራሮች የወ/ት ብርቱካንን መታሰር በመቃወም ሚያዝያ አንድ ቀን ሠላማዊ ሰልፍ ያካሂዳሉ

Ethiopia Zare (ሰኞ መጋቢት 28 ቀን 2001 ዓ.ም. April 6, 2009)፦ በአዲስ አበባ የሚገኙ የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ አመራር አባላትና የአጋር ፓርቲ መሪዎች “ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ የታሰሩበት የሕግ አግባብ ትክክል አይደለም” በሚል የፊታችን ሐሙስ ሚያዝያ 1 ቀን 2001 ዓ.ም. ሠላማዊ ሰልፍ ሊያካሂዱ መሆኑን ፓርቲው ለጋዜጠኞች በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የወ/ሮ አዜብ መስፍን ለኤፈርት ም/ሥራ አስኪያጅ ሆነው መሾም ቅሬታ አስነሳ

Ethiopia Zare (ሰኞ መጋቢት 28 ቀን 2001 ዓ.ም. April 6, 2009)፦ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን የህወሓት የሆነው (ኤፈርት) ምክትል ሥራ አስኪያጅ ሆነው መሾም በፓርቲው አመራሮች መካከል ቅሬታ መፍጠሩን ምንጮች ጠቆሙ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንድ ፌደራል ፖሊስ አንድ ገድሎ፣ ሁለት ባልደረቦቹን አቁስሎ፣ ራሱን ገደለ

- ሁለት የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ሠራተኞች ተጎድተዋል

Ethiopia Zare (እሁድ መጋቢት 27 ቀን 2001 ዓ.ም. April 5, 2009)፦ አራት ኪሎ የሚገኘውን ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት በመጠበቅ ላይ የሚገኙ ፌደራል ፖሊሶች ባደረጉት ግምገማ ያልተደሰተ አንድ አባላቸው ሦስቱ ላይ ተኩሶ ከጣላቸው በኋላ ራሱን አጠፋ። አንዱ ሲሞት አንዱ በሞት አፋፍ ላይ እንደሚገኙና አንዱ መቁሰሉ ታውቋል። ሁለት የማተሚያ ቤቱ ሠራተኞችም ጉዳት ደርሶባቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በፓሪሱ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ

Paris Marathon, 20090405በሴቶች አንደኛና ሁለተኛ፣ በወንዶች ሁለተኛ ሆነዋል

Ethiopia Zare (እሁድ መጋቢት 27 ቀን 2001 ዓ.ም. April 5, 2009)፦ በ33ኛው የፓሪስ ማራቶን ኢትዮጵያውያኖቹ ሴት አትሌቶች አፀደ ባይሳ እና አሰለፈች መርጊያ አንደኛና ሁለተኛ ሲወጡ፣ በወንዶች ደግሞ አትሌት በዙ ወርቁ ኬንያዊውን ቪንሰንት ኪፐሩቶን ተከትሎ ሁለተኛ ወጥቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ማረሚያ ቤቶች ከተቃውሞ በቀር በወ/ት ብርቱካን ክስ ላይ ምላሽ አልሰጠም

የማረሚያ ቤቶችና የወ/ት ብርቱካን ጠበቃ ሙሉ የፍርድ ቤት ሙግት

W/t Birtukan MideksaEthiopia Zare (እሁድ መጋቢት 27 ቀን 2001 ዓ.ም. April 5, 2009)፦ ልደታ አካባቢ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግቢ ውስጥ በሚገኘው የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዘጠነኛ ፍትሐብሔር ችሎት መግቢያ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ተጨናንቋል። ከዚህ ቀደም በዚህ ችሎት ሁለትና ሦስት ሆነው ከሚመጡ ባለጉዳዮች ውጭ እንዲህ ቁጥሩ በርከት ያለ ታዳሚ ታይቶ አይታወቅም። ከችሎቱ መግቢያ ፊት ለፊት ላይ ሰዎች ሦስትና አራት ሆነው በመሰባሰብ የየራሳቸውን ውይይት ይዘዋል። የወ/ት ብርቱካን እናት ነጠላቸውን ተከናንበው ከአንዱ ጥግ ተቀምጠው የሚሆነውን ይጠባበቃሉ። ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው፣ ዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማርያም፣ ዶ/ር ኃይሉ አርኣያ፣ አቶ አክሉ ግርግሬ፣ አቶ አስራት ጣሴና ሌሎች የአንድነት ፓርቲ ሰዎችም ተገኝተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፍቅርአዲስ ከ”ጠንቋዩ” ጋር በተያያዘ ስሟን ያነሱ ጋዜጦችን አስጠነቀቀች

Fkereaddis NeqatibebeEthiopia Zare (እሁድ መጋቢት 27 ቀን 2001 ዓ.ም. April 5, 2009)፦ ከአሥር ዓመታት በላይ ”ባለአውሊያ” እና ”ባለከራማ” እንደሆነ በመግለጽ በርካታ ተከታዮችን አፍርቶ የነበረውና በስድስት ሰዎች ሞት፣ ሰዎችን በማታለልና ሴቶችን በመድፈር ወንጀል በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሎ ጉዳዩ በፍርድ ቤት እየታየ ያለው አቶ ታምራት ገለታ የተባለው ”ጠንቋይ” ደንበኛ መሆኗን የዘገቡ ጋዜጦችን ፍርድ ቤት እንደምትገትር አርቲስት ፍቅርአዲስ አስጠነቀቀች። አርቲስት ማንአልሞሽ ዲቦ ታማ በሕክምና ላይ ብትሆንም የትም ቦታ መሄድ መብቷ መሆኑን በመግለጽ ወንድሟ ማስተባበያ ሰጥቷል። ማስተባበያው ግን ”የተባለውን ብትሰማ ታብዳለች” የሚል ሌላ ማስተባበያ ተሰጥቶበታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለመጀመሪያ ጊዜ ቅዳሜ ችሎት ሊሰየም ነው

ጉዳዩም የ”ጠንቋይ” ታምራት ነው

Ethiopia Zare (እሁድ መጋቢት 27 ቀን 2001 ዓ.ም. April 5, 2009)፦ ”በጥንቆላ መሥሪያ ቤቶቹ” ከሌሎች ስድስት ተባባሪዎቹ ጋር በመሆን ”ባለአውሊያ” እና ”ባለከራማ” ነኝ በማለት የሰው ግድያ ወንጀልና ከባድ ማታለል ፈጽሟል በሚል በአቶ አቶ ታምራት ገለታ እና በተባሪዎቹ ላይ ክስ ያቀረበው ዓቃቤ ሕግ ያሉን የሰው ምስክሮችና የሰነድ ማስረጃዎች አቅርቤ ጨርሻለሁ የቀረኝ የቪዲዮ ማስረጃ ነው በማለቱ፤ በፍርድ ቤት ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ቅዳሜ ዕለት ተሰይሞ በዝግ ችሎት ቪዲዮ ካሴት ሊመለከት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ራሱን የገደለው ባለሀብት ንብረት በ58.5 ሚሊዮን ብር ዕዳ ሊሸጥ ነው

Ethiopia Zare (ማክሰኞ መጋቢት 22 ቀን 2001 ዓ.ም. March 31, 2009)፦ ከወራት በፊት ራሳቸውን ከገደሉት ባለሀብቶች ውስጥ የ”ጌታነህ ትሬዲንግ” ባለቤት የነበሩትን የአቶ ዮሐንስ ጌታነህ ንብረት አቢሲኒያ ባንክ በ58 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ዕዳ የሐራጅ ሽያጭ አወጣበት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...