መንግሥት የሁለቱን የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ (VOA) ጋዜጠኞች ፈቃድ ቀማ

ከሣምንት በኋላ ጠይቁን ተብለዋል

Ethiopia Zare (ዓርብ ሚያዝያ 9 ቀን 2001 ዓ.ም. April 17, 2009)፦ በ1997 ዓ.ም. ምርጫ ወቅት ተቀጥረው ሥራ የጀመሩት መለስካቸው አምሃ እና እስክንድር ፍሬው የተባሉት የአሜሪካ ድምፅ ጋዜጠኞች ከኢትዮጵያ መንግሥት የተሰጣቸውንና መዘገብ የሚያስችላቸውን ፈቃድ መቀማታቸውን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ። መንግሥት በአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ዘገባ አለመደሰቱን ከመግለጽ ውጭ የተባሉት ነገር የለም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወ/ት ብርቱካን እንዲፈቱ የሚጠይቀው ሰልፍ ያለውጤት ተመለሰ

UDJ rally in Addis Ababa, 2009,04,16

Ethiopia Zare (ሐሙስ ሚያዝያ 8 ቀን 2001 ዓ.ም. April 16, 2009)፦ ከምርጫ 97 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የተፈቀደውን ሠላማዊ ሰልፍ ለማድረግ የአንድነት አመራሮች ዛሬ ሐሙስ ሚያዝያ 8 ቀን 2001 ዓ.ም. ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት ጀምሮ ነበር በአንድነት ቢሮ መሰባሰብ የጀመሩት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፖሊስ ሠራዊት አባላት በመንግሥት ድርጊት ተማረዋል

Ethiopia Zare (ሐሙስ ሚያዝያ 8 ቀን 2001 ዓ.ም. April 16, 2009)፦ በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ አያሌ የፌደራሉ መንግሥት እና የመዲናይቱ ፖሊስ አባላት ከደምወዝ ክፍያ ማነስ ጋር በተያያዘ ሥርዓቱን እያማረሩ መሆናቸው ታወቀ። ከመካከላቸውም "በኢትዮጵያ የሥርዓት ለውጥ ያስፈልጋል፣ በወገናችን እየተጠላን መኖሩ ታክቶናል፣ የእኛም ሆነ የኢትዮጵያ ህዝብ ሕይወት በቃላት ድርደራ ካልሆነ በቀር በተግባር አልተለወጠም" በማለት መንግሥቱን የሚያማርሩ እንዳሉም ምንጮች አረጋግጠዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአንድነት ፓርቲ ሠላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው

'ታጋይን በማሰር ትግልን ማቆም አይቻልም!' ሰልፈኞች

ህዝብ በየቦታው ቆሞ እየተከታተለ ነው

Ethiopia Zare (ሐሙስ ሚያዝያ 8 ቀን 2001 ዓ.ም. April 16, 2009)፦ ዛሬ ጠዋት የጀመረው የአንድነት ፓርቲ ሠላማዊ ሰልፍ ብዛት ያላቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በቅርበት እየተከታተሉት ከመሆኑም በላይ በአሁኑ ሰዓት በቤተመንግሥት አካባቢ በከፍተኛ ድምፅ መፈክሮችን እያሰሙ መሆኑን በስፍራው የሚገኙ የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በወ/ት ብርቱካን ክስ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ሙሉ ቃል

Ethiopia Zare (ሐሙስ ሚያዝያ 8 ቀን 2001 ዓ.ም. April 16, 2009)፦ በእስር ላይ ያሉት የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ሊቀመንበር ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ብቻዬን በመታሰሬ የሰብዓዊ ክብሬ ተገፏል ብለው ያቀረቡትን ጥያቄ ፍርድ ቤቱ ውድቅ ማድረጉን ትናንት መዘገባችን አይዘነጋም። ማረሚያ ቤቱ ከሌሎች እስረኞች ጋር እንዳይገናኙ አድርጎ ብቻቸውን የማሰር ሥልጣን አለው ሲል የፌደራል የመጀመሪ ደረጃ ፍርድ ቤት ዘጠነኛ ችሎት ውሳኔ የሰጠ ሲሆን፤ ለሁለተኛው ክስ "በቅርብ ጓደኞቻቸው፣ ዘመዶቻቸው እንዲሁም በሐኪማቸው፣ የሕግ ባለሙያ እና በኃይማኖት አባት የመጎብኘት መብት ባለቤት መሆናቸው በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 21 እና በሚንስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 138/99 አንቀጽ 13 ላይ ስለተረጋገጠ ተከሳሽ ለሌሎች እስረኞች ይህንን በሚያከብርላቸው መልክ የከሳሽንም እነዚህ መብቶችን እንዲያከብርና በከሳሽ ላይ የጣለው ክልከላ እንዲነሳ ተወስኗል" በማለት መዝገቡን ዘግቷል። የውሳኔውን ሙሉ ቃል እንደሚከተለው አቅርበነዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወ/ት ብርቱካን የመጎብኘት መብቷ በፍርድ ቤት ተረጋገጠ

ማረሚያ ቤቱ እስረኛዋን ለብቻዋ ማሰር ይችላል ተብሏል

Ethiopia Zare (ረቡዕ ሚያዝያ 7 ቀን 2001 ዓ.ም. April 15, 2009)፦ ለሦስት ወራት ከ17 ቀን ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ በታጣቂዎች ታፍና ወደ ቃሊቲ እስር ቤት የተጣለችው ብቸኛዋ የሴት የፖለቲካ መሪ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ በጠበቃዋ፣ በሐኪሟ፣ በኃይማኖት አባቷ፣ በቤተሰቦቿ፣ በወዳጅ ዘመዶቿና በጓደኞቿ የመጎባኘት መብቷ የተረጋገጠ መሆኑን ዛሬ በአዲስ አበባ የተሰየመው የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ውሳኔ መስጠቱ ታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንድነት የወ/ት ብርቱካንን እስር በመቃወም የጠራው ሠላማዊ ሰልፍ ተፈቀደ

ሰልፉ ነገ ጠዋት ይደረጋል

Ethiopia Zare (ረቡዕ ሚያዝያ 7 ቀን 2001 ዓ.ም. April 15, 2009)፦ የዓለም ፓርላማ አባላቶች ስብሰባ በአዲስ አበባ ይካሄዳል በሚል ምክንያት ተሰርዞ የነበረው የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የወ/ት ብርቱካንን እስር በመቃወም ያዘጋጀው የሠላማዊ ሰልፍ ተፈቅዶ፤ ነገ ሚያዝያ 8 ቀን 2001 ዓ.ም. (April 16, 2009 እ.ኤ.አ.) ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ እንደሚካሄድ የአዲስ አበባ ምንጮቻችን አረጋገጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወ/ት ብርቱካንን ለማየት ከአውሮፓ የተጓዙት የፓርላማ አባል እንዳይጎበኟቸው ተከለከሉ

Carina Häggየኢህአዲግ መንግሥት ባለሥልጣናትን ለማነጋገር ያደረጉት ጥረት አልተሳካም

Ethiopia Zare (ኀሙስ ሚያዝያ 1 ቀን 2001 ዓ.ም. April 9, 2009)፦ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበር ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ የሚገኙበትን ሁኔታ ለማየት ወደ ኢትዮጵያ ያቀኑት የስዊድን የሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ የፓርላማ አባል የሆኑት ካሪማ ሄግ ወ/ት ብርቱካንን ለማነጋገርም ሆነ ለማየት ተከለከሉ። የወ/ት ብርቱካንን እናት እና ልጅን አግኝተው ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ወስነዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሁለቱ አንጋፋ ተቃዋሚዎች እንደተለመደው ወንበሩን ተቀያየሩት

Dr. Merera & Prof. Beyene
 

Ethiopia Zare (ኀሙስ ሚያዝያ 1 ቀን 2001 ዓ.ም. April 9, 2009)፦ ተቃውሞአቸውን ባሰሙ ቁጥር የአቶ መለስን ሥልጣን የሙጥኝ ማለት ደጋግመው የሚያስታውሱን ሁለቱ አንጋፋ ተቃዋሚዎች የፓርቲያቸውን ወንበር ለዓመታት እየተቀያየሩ ያለተተኪ መቀጠላቸውን አላቋራጡም። የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎች ኅብረት (ኢዴኃኅ) ባካሄደው አራተኛ መደበኛ ጉባዔ ዶ/ር መረራ ጉዲና፣ ሊቀመንበር ፕሮፌሠር በየነ ጴጥሮስ ተቀዳሚ ም/ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...