“ባህላችን ለባርነት እንድንመቻች አድርጎናል” ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም

Ethiopia Zare (ሰኞ መጋቢት 21 ቀን 2001 ዓ.ም. March 30, 2009)፦ ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም በስዊድንና በአካባቢው ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጋር ቅዳሜ መጋቢት 19 ቀን 2001 ዓ.ም. በስቶክሆልም ከተማ በኢትዮጵያ ወቅታዊና ታሪካዊ ጉዳዮች ላይ ሰፋ ያለ ውይይት አድርገዋል። ውይይቱ የተለያዩ ሃሳቦች የተንሸራሸሩበት፣ ትምህርታዊ፣ አዝናኝና ታሪካዊ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አነጋጋሪው የጠንቋዩና የግብረአበሮቹ ክስ

ጠንቋዩና ስድስት ግብረአበሮቹ የተከሰሱት በ9 ሰዎች ሕይወት ማጥፋት፣ የሰው ገንዘብና ንብረት በማታለልና በማጭበርበር፣ ሴቶችን በመድፈር ነው

ከዕድሜ ልክ እስራት እስከ የሞት ቅጣት ሊቀጡ ይችላሉ

ጠንቋዩን ታዋቂ ግለሰቦችና ባለሥልጣኖች ያመልኩታል

ማንአልቦሽ ዲቦ፣ ብርቱካንና የሺመቤት ዱባለ፣ ፍቅርአዲስ ነቃጥበብ ደንበኞቹ ነበሩ

Ethiopia Zare (ዓርብ መጋቢት 18 ቀን 2001 ዓ.ም. March 27, 2009)፦ ከአሥር ዓመታት በላይ ”ባለ አውሊያ” እና ”ባለ ከራማ” እንደሆነ በመግለጽ በርካታ ተከታዮችን አፍርቶ የነበረውና በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሎ ጉዳዩ በፍርድ ቤት እየታየ ያለው አቶ ታምራት ገለታ የተባለው ”ጠንቋይ” ጉዳይ በመዲናዋ አዲስ አበባና በመላው ኢትዮጵያ የሰሞኑ የመነጋገሪያ አጀንዳ (Hot issue) ሆኗል። መነጋሪያነቱ የጨመረው ታዋቂ አርቲስቶች፣ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ አትሌቶች፣ የመከላከያ ሠራዊት አባላት፣ ታዋቂ ባለሀብቶችና የኃይማኖት አባቶች በጥንቆላ ቤቶቹ ተጠቃሚ ነበሩ የሚሉ ምስክሮች ፍርድ ቤት በመቅረባቸው ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መኢአድ መድረክን ለመቀላቀል ጥያቄ አቀረበ

Ethiopia Zare (ዓርብ መጋቢት 18 ቀን 2001 ዓ.ም. March 27, 2009)፦ በኢንጅነር ኃይሉ ሻውል የሚመራው የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) መድረክ ለዲሞክራሲያዊ ምክክር በኢትዮጵያ (መድረክን) ለመቀላቀል ጥያቄ ማቅረቡን የኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአፍሪካ ቀንድ ሀገሮች ወቅታዊና መፃይ ጉዳዮች ላይ ሴሚናር ተካሄደ

Prof. Mesfin W.Mariam, 090326 Sweden (Photo S)ፕ/ር መስፍን በቀንዱና በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ጽሑፍ አቀረቡ

Ethiopia Zare (ዓርብ መጋቢት 18 ቀን 2001 ዓ.ም. March 27, 2009)፦ በአፍሪካ ቀንድ በሚገኙት ኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ ሶማሊያና ጅቡቲ ሀገሮች ላይ ባተኮረውና ኀሙስ መጋቢት 17 ቀን በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም በተደረገ የአንድ ሙሉ ቀን ሴሚናር ላይ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳና ጋዜጠኛ ዳዊት ይስኃቅ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷቸው ነበር። ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም በሁለት ርዕሰ ጉዳዮ ጽሑፍ አቀረቡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፕ/ር መስፍን ከስዊድን የውጭ ጉዳይ ሚ/ር የአፍሪካ ኃላፊ ጋር ተወያዩ

Ethiopia Zare (ኀሙስ መጋቢት 17 ቀን 2001 ዓ.ም. March 26, 2009)፦ ፕሮፌሠር መስፍን ወልደማርያም ከስዊድን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ባለሥልጣናት፣ ከመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ከፓርላማ አባላት ጋር በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ረቡዕ መጋቢት 16 ቀን 2001 ዓ.ም. ተወያዩ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንድነት ፓርቲ ህዝባዊ ስብሰባ ሊያካሂድ ነው

በቅርቡም ህዝባዊ ሰልፍ እንደሚጠራ ታወቀ

Ethiopia Zare (ረቡዕ መጋቢት 16 ቀን 2001 ዓ.ም. March 25, 2009)፦ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የፊታችን ቅዳሜ መጋቢት 20 ቀን 2001 ዓ.ም. ታላቅ የህዝብዊ ስብሰባ እንደሚጠራና ከህዝብ ጋር የሕግ የበላይነት መከበርን አስመልክቶ ሰፊ ውይይት በኢምፔሪያል ሆቴል እንደሚያካሂድ ከአዲስ አበባ የደረሰን መረጃ ጠቆመ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ውይይት ለሰላምና ለጋራ አላማ በኢትዮጵያ

ታላቅ የስብሰባ ጥሪ በዋሽንግተን ዲሲ

Ethiopia Zare (ረቡዕ መጋቢት 16 ቀን 2001 ዓ.ም. March 25, 2009)፦ ባለፈው ዓመት መጨረሻ የተጀመረውና በዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ በየሶስት ወሩ የሚደረገው የውይይት መድረክ ቀጣይ የውይይት ርእሶችን በማዘጋጀት ለሁለተኛ ጊዜ ታላቅ የውይይት መድረክ ማዘጋጀቱ ተገለጸ። የመጀመሪያው ውይይት “ከፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ የፕራዜዳንታዊ ውድድር ኢትዮጵያዊያን ምን ልንማር እንችላለን?” የሚል ነበረ ሲሆን በስብሰባው ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸው እንደነበር አይዘነጋም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፕሮፌሠር መስፍን ወ/ማርያም ስዊድን ገቡ

ቅዳሜ ማርች 28 በስቶክሆልም ከኢትዮጵያውያን ጋር ይወያያሉ

By Matias Ketema

Prof. Mesfin WoldemariamEthiopia Zare (ሰኞ መጋቢት 14 ቀን 2001 ዓ.ም. March 23, 2009)፦ የስዊድን የሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ እና የኡሎፍ ፓልመ ኢንስቲትዩት በጋራ ባደረጉላቸው ግብዣ መሰረት በአፍሪካ ቀንድ ፖለቲካ ጉዳይ ላይ በሚደረግ ስብሰባ ላይ ገለፃና ማብራሪያ ለመስጠት ፕሮፌሠር መስፍን ወልደማርያም ዛሬ ስዊድን ዋና ከተማ ስቶኮልም ገብተዋል። የፊታችን ቅዳሜ ማርች 28 ቀን በስቶክሆልም ከኢትዮጵያውያንን ጋር ህዝባዊ ውይይት ያደርጋሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአንድነት ፓርቲ አመራሮች የአሜሪካ አምባሳደርን አነጋገሩ

‘የፖለቲካ እንቅስቃሴው አደጋ ላይ ነው’ ዶ/ር ኃይሉ አርኣያ

Ethiopia Zare (ሐሙስ መጋቢት 10 ቀን 2001 ዓ.ም. March 19, 2009)፦ አራት የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ በኢትዮጵያ የአሜሪካን አምባሳደርና የፖለቲካ ክፍል ኃላፊ ጋር ሰፊ ውይይት ማድረጋቸውን የኢትዮጵያ ዛሬ ሪፖርተር ዘገበ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...