‘የሻማ መብራት ስነሥርዓቱ የተሳካ ነበር’ ዶ/ር ኃይሉ አርኣያ

ዶ/ር ያዕቆብ ታስረው ተፈቱ

አቶ ተመስገን በደቡብ አንድ ጽ/ቤት መዘጋቱን አረጋገጡ

Ethiopia Zare (ረቡዕ ጥር 20 ቀን 2001 ዓ.ም. January 28, 2009)፦ የአንድነት ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባላት፣ የብሔራዊ ምክር ቤት አባላትና የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ጋዜጠኞች የተገኙበት ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ለእስር የተዳረገችበትን አንደኛ ወር በማሰብ በፓርቲው ጽ/ት ቤት የሻማና የጧፍ ማብራት ስነሥርዓት ተካሄደ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

"ብርቱካን ትፈታ" የሻማ መብራት በአዲስ አበባ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ጥር 19 ቀን 2001 ዓ.ም. January 27, 2009)፦ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበር ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ የታሰረችበትን አንደኛ ወር በአጋርነት በማሰብ የሻማ መብራትና የግጥም ስነሥርዓርት ነገ በፓርቲው ጽሕፈት ቤት ይካሄዳል። ፕሮፌሠር መስፍን ጽሑፍ ያቀርባሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፕሬዝዳንት ባራክ ሁሴን ኦባማ ሥልጣን ተረከቡ

ያሬድ ክንፈ (ከዋሽንግተን ዲሲ)

Obama swearing, 2009,01,20

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ጥር 12 ቀን 2001 ዓ.ም. January 20, 2009)፦ በዋሽንግተን ዲሲ ሰዓት አቆጣጠር ከቀኑ ስድስት ሰዓት ከአምስት ደቂቃ (12:05 P.M.) አካባቢ ሴናተር ባራክ ኦባማ ቃለ መኀላ በመፈጸም አርባ አራተኛው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሆነዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከታሪካዊው ደቂቃ በፊት

ያሬድ ክንፈ (ከዋሽንግተን ዲሲ)

Tuesday: President-elect Barack Obama and his wife, Michelle, flank President and Mrs. Bush at the White House (AP Photo).

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ጥር 12 ቀን 2001 ዓ.ም. January 20, 2009)፦ ዛሬ ማክሰኞ ጥር 12 ቀን 2001 ዓ.ም. የአሜሪካን ዋና ከተማ የሆነችው ዋሽንግተን ዲሲ ከመቼውም ጊዜ በላይ በህዝብ የተጨናነቀችበት ዕለት ነው። የዓለም ህዝቦች ዓይንና ጆሮም በዚህችው ከተማ ላይ አነጣጥረዋል። አሜሪካ ፕሬዝዳንቷን የምትቀይርበት ዕለት ነውና።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቀልቤሳ ነገዎ በድጋሚ ጥፋተኛ ተባሉ

Ethiopia Zare (ዓርብ ጥር 8 ቀን 2001 ዓ.ም. January 16, 2009)፦ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በደርግ ሥርዓት ከቀይ ሽብር ጋር በተያያዘ በዘር ማጥፋት ወንጀል ዓቃቤ ሕግ ክስ መስርቶባቸው የነበሩትንና በሌሉበት የዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸው የነበሩትና ጉዳያቸው በድጋሚ ሲታይላቸው የቆዩት አቶ ቀልቤሳ ነገዎ ረቡዕ ጥር 6 ቀን በዋለው ችሎት “ጥፋተኛ” ተብሎ ተፈረደባቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በስዊድን የተደረገው ሰልፍ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ

በማትያስ ከተማ

Ethiopia Zare (ኀሙስ ጥር 7 ቀን 2001 ዓ.ም. January 15, 2009)፦ ረቡዕ የካቲት 6 ቀን 2001 ዓ.ም. ተለዋዋጩን የስዊድን የአየር ሁኔታ ደፍሮ ለመናገር ባያስተማምንም ዕለቱ ከሰልፈኛው ጋር የተባበረ ይመስል ነበር። በስቶክሆልም ዝናብ አልነበረም። በስዊድን ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያን ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ ሊገናኙ ከተቃጠሩበት በስቶክሆልም በሰርገልስ ቶርየት አደባባይ የደረስኩት ከሰዓቱ ቀደም ብዬ ነበር። በቦታው ላይ መጠነኛ ሰዎች የነበሩ ሲሆን ቀስ በቀስ ግን አደባባዩ ባንዲራ በለበሱ ባነገቱና በተከናነቡ ልዩ ልዩ ጽሑፎችና ፎቶዎች በያዙ ኢትዮጵያውያን ተሞላ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሲያትሉ ሰልፍ ዘገባ

ብርቱካን ሚደቅሳ ትፈታ! አቶ በቀለ ጅራታ ይፈቱ! ቴዲ አፍሮ ይፈታ!

Ethiopia Zare (ኀሙስ ጥር 7 ቀን 2001 ዓ.ም. January 15, 2009)፦ የተለያዩ መፈክሮችን በማሰማት ትላንት የሲያትል እምብርት ከሆነው ዌስት ሌክ ሴንተር የተጀመረውና በሲያትል የፌደራሉ መንግሥት መቀመጫ በሆነው ፌደራል ሐውስ የተጠናቀቀው የሲያትል፣ የቫንኩቨርና የፖርት ላንድ ነዋሪዎች ያካሄዱት ሰልፍ በስኬት መጠናቀቁ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለዓለም አቀፉ የተቃውሞ ሰልፍ ቅድመ ሁኔታ መጠናቀቁ ተገለጸ

በማትያስ ከተማ

Ethiopia Zare (ሰኞ ጥር 4 ቀን 2001 ዓ.ም. January 12, 2009)፦ የወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳን፣ የአርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁንን፣ የአቶ በቀለ ጅራታን እንዲሁም በፖለቲካ ምክንያት በእስር እየማቀቁ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን እንዲፈቱ የሚጠይቀውንና ረቡዕ ጥር 6 ቀን (January 14) ለሚካሄደው ዓለም አቀፍ የተቃውሞ ሠልፍ በስዊድን ቅድመ ሁኔታው መጠናቀቁ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በወ/ት ብርቱካን እስር ዙሪያ የተጠናከረ ዘገባ

W/o Almaz G/Egziabeher“ሰው ገብቶ እንዲጠይቃት ይፈቀድልኝ” ወ/ሮ አልማዝ ገ/እግዚአብሔር የወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ እናት

ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ማኅበር ወ/ት ብርቱካንን እንዳይጎበኝ ተከለከለ

ወ/ት ብርቱካን የታሰሩት የአንድነት ፓርቲን እንቅስቃሴ ለማዳከም ታስቦ ነው

የእንግሊዝ ኤምባሲ የወ/ት ብርቱካን እስር እንዳሳሰበው ገለፀ

“የሕገመንግሥቱ አንቀጽ 21 ሊከበርላቸው ይገባል” አቶ አበበ ወርቄ የኢሰመጉ ሊቀመንበር

መድረክ የወ/ት ብርቱካንን መታሰር አስመልክቶ ያወጣው መግለጫ 

Ethiopia Zare (ሰኞ ጥር 4 ቀን 2001 ዓ.ም. January 12, 2009)፦ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ሊቀመንበር፣ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ እናት የ72 ዓመቷ ወ/ሮ አልማዝ ገ/እግዚአብሔር፣ “በሕግ ስለተያዘው ጉዳይና ስለፖለቲካ የማውቀው ጉዳይ የለኝም፤ ግን ለሌላው እንደተፈቀደው ለልጄም ሰው ገብቶ እንዲጠይቃት ይፈቀድልኝ” ሲሉ መንግሥትን ተማፀኑ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...