የወ/ት ብርቱካን ጠበቃ ክስ ተቀባይነት አገኘ

ወ/ት ብርቱካን ፍርድ ቤት አልቀረበችም

Ethiopia Zare (ሐሙስ መጋቢት 10 ቀን 2001 ዓ.ም. March 19, 2009)፦ ከታህሳስ 20 ቀን 2001 ዓ.ም. ጀምሮ ለሰማኒያ ቀናት በአንድ ጠባብ ክፍል ውስጥ በእስር ላይ የምትገኘው የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ከወዳጅ ዘመዶቿና ከጠበቃዋ ጋር እንዳትገናኝ ከመደረጉም በላይ በእስር ቤት የሰብዓዊ መብት አያያዛዟ ሁኔታ አግባብ አይደለም ሲል ጠበቃዋ ማረሚያ ቤቱን በመጀመሪያ ደረጃ የልደታ ፍርድ ቤት የከሰሰ ሲሆን፤ ፍርድ ቤቱም ትላንት ረቡዕ መጋቢት 9 ቀን በዋለው ችሎት ክሱ ተቀባይነት እንደገኘ ታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለካናዳ ምክር ቤት የሚሰጥ የድጋፍ ደብዳቤ እየተፈረመ ነው

ብርቱካን ሚደቅሳ ትፈታ!!

Ethiopia Zare (ሐሙስ የካቲት 26 ቀን 2001 ዓ.ም. March 5, 2009)፦ የብርቱካን ሚደቅሳን መታሰር በመቃወም ካናዳ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያኖችና ጉዳዩ ያሳሰባቸው ሀገር ወዳዶች ለካናዳ ምክር ቤት (THE CANADIAN HOUSE OF COMMONS) የሚሰጥ የድጋፍ ማሰባሰቢያ ደብዳቤ በመፈረም ላይ መሆናቸው ታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በስዊድን የተደረገው ሰልፍ በተሳካ ሁኔታ ተካሄደ

World Rally, Sweden 02032009By Matias Ketema

Ethiopia Zare (ማክሰኞ የካቲት 24 ቀን 2001 ዓ.ም. March 3, 2009)፦ የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር የሆኑትን የወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳን አላግባብ መታሰር በመቃወም ትናንት ሰኞ የካቲት 23 ቀን በዓለም አቀፍ ሁኔታ የተዘጋጀው ሰልፍ በስዊድን ዋና ከተማ በስቶክሆልም በተሳካ ሁኔታ ተካሄደ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አለም አቀፍ ተቃውሞ ሰልፍ ተካሄደ

Ethiopia Zare (ሰኞ የካቲት 23 ቀን 2001 ዓ.ም. march 2,  2009)በቅርቡ ወደ እስር የተጣለችውን አንድነት ፓርቲ ሊቀመንበርን ጨምሮ ያለፍትህ በእስር ቤት የሚገኙ የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ ዘንድ የሚጠይቀው በውጭ ሀገር የሚገኙ ኢትዮጵያዊያኖች ዛሬ ሰኞ በተለያዩ ሀገራት ዋና ዋና ከተሞች የተቃውሞ ሰልፍ እያካሄዱ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

”አራት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን ህዝብ ተርቧል” የኢትዮጵያ መንግሥት

"ከ602 ሚሊዮን ዶላር በላይ ለምግብ መግዣ ያስፈልጋል" አቶ ምትኩ ካሣ (የግብርናና ገጠር ልማት ሚኒስትር ዴኤታ)

Ethiopia Zare (ማክሰኞ የካቲት 17 ቀን 2001 ዓ.ም. February 24, 2009)፦ በኢትዮጵያ አራት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን ህዝብ መራቡን በዛሬው ዕለት የገለፀው የኢትዮጵያ መንግሥት፤ ከ602 ሚሊዮን ዶላር በላይ ለምግብ መግዣ እንደሚያስፈልገው አስታውቋል። ከዚህ ውስጥ 148 ሚሊዮን ዶላር በእጁ እንደሚገኝና፣ 455 ሚሊዮን ዶላሩን ከለጋሾች እንደሚጠብቅ ይፋ አደረገ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አትሌት መሰረት ደፋር በአምስት ሺህ ሜትር ክብረወሰን ሰበረች

Athlete Meseret Defar, Photo: Hasse Sjögrenበጥሩነሽ ዲባባ ተይዞ የነበረውን ክብረወሰን ከሦስት ሰከንድ በላይ አሻሻለችው

Ethiopia Zare (ረቡዕ የካቲት 11 ቀን 2001 ዓ.ም. February 18, 2009)፦ በዛሬው ዕለት ማምሻውን በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም ውስጥ በግሉበን በተካሄደው የሴቶች የአምስት ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር ኢትዮጵያዊትዋ አትሌት መሰረት ደፋር ውድድሩን በ14 ደቂቃ ከ24፡37 ሰከንድ በአንደኝነት በመጨረስ የዓለምን ክብረወሰን ሰበረች። ክብረወሰኑን ያሻሻለችው በሦስት ነጥብ አምስት ሰከንድ ነው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቴዲ አፍሮ ከሦስት ወር በኋላ ሊፈታ ይችላል

Teddy Afroፍርዱ ከስድስት ዓመት ወደ ሁለት ዓመት ተቀየረ

Ethiopia Zare (ረቡዕ የካቲት 11 ቀን 2001 ዓ.ም. February 18, 2009)፦ ዛሬ የጠቅላይ ፍርድ ቤት የይግባኝ ሰሚ ችሎት በአርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን ላይ ተጥሎ የነበረውን የስድስት ዓመት እስራት አሻሽሎ ወደ ሁለት ዓመት ጽኑ እስራት እንዲጸና ውሳኔ ማሳለፉን የአዲስ አበባ ሪፖርተራችን ከስፍራው ዘገበ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወ/ት ብርቱካን በሦስተኛ ሰው እንዳትጠየቅ ተከለከለ

‘ለአክስቷ ልጅ የተፈቀደው በስህተት ነው’ ፖሊስ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ የካቲት 03 ቀን 2001 ዓ.ም. February 10, 2009)፦ ከሽማግሌዎቹ አንዱ በሆኑት ፓስተር ዳንኤል ቢሮ ስትወጣ በታጠቁ ሰዎች ተይዛ ወደ እስር ከተጣለች 41ኛ ቀኗን ያስቆጠረችው የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ሊቀመንበር ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ በአክስቷ ልጅ እንዳትጎበኝ ተከለከለች። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለወ/ት ብርቱካን ቤተሰቦች መርጃ 5000 ዶላር ተሰበሰበ

የቫንኩቨር ሴቶች ብርቱካንን አልረሷትም

Ethiopia Zare (ሰኞ የካቲት 02 ቀን 2001 ዓ.ም. February 9, 2009)፦ ትናንት እሁድ ፌብርዋሪ 8 ቀን በቫንኩቨር ካናዳ የሚኖሩ ሴቶች ለወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ እናትና ለሕፃን ልጇ መርጃ ይሆን ዘንድ ባዘጋጁት የገንዘብ ማሰባሰቢያ ምሽት አምስት ሺህ የካናዳ ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አሰባሰቡ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የቫንኩቨር ነዋሪዎች የሻማ ማብራት ስነሥርዓት አካሄዱ

ወ/ት ብርቱካንና ሌሎች የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ ጠይቀዋል

Ethiopia Zare (ሰኞ ጥር 25 ቀን 2001 ዓ.ም. February 2, 2009)፦ የቫንኩቨር ካናዳ ነዋሪዎች በቃሊቲ እስር ቤት 37ኛ ቀን የሆናትን የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበርን ጨምሮ ሌሎች የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ በመጠየቅ በከተማዋ እምብርት በሆነው ሮብሰን ስትሪት በመሰባሰብ የሻማ ማብራት ስነሥርዓት አካሄዱ። ለህሊና እስረኞቹም አጋርነታቸውን በማሳየት በየሀገራቱ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን በሚኖሩበት ቦታ ላሉ የመንግሥት አካላት በተደጋጋሚ በመሄድ የእስረኞቹን ሁኔታ እንዲያስረዱ ባወጡት መግለጫ ጥሪ አቀረቡ። ሙሉውን አስነብበኝ ...