የእነአቶ ጃዋር መሐመድና የቅርብ ቤተሰቦች የባንክ አካውንት ታገደ
“አካውንቶቹ የታገዱት በሕጋዊ መንገድ ነው” ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ
ኢዛ (ዓርብ ሐምሌ ፳፬ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. July 31, 2020)፦ ከአርቲስት ሐጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር ተያይዞ በቅርቡ በተፈጠረው ቀውስ ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የሚገኙት የእነአቶ ጃዋር መሐመድ የባንክ አካውንት መታገዱ ታወቀ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ዓርብ ሐምሌ ፳፬ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. July 31, 2020)፦ ከአርቲስት ሐጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር ተያይዞ በቅርቡ በተፈጠረው ቀውስ ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የሚገኙት የእነአቶ ጃዋር መሐመድ የባንክ አካውንት መታገዱ ታወቀ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ዓርብ ሐምሌ ፳፬ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. July 31, 2020)፦ ካለፉት ሦስት ሳምንታት ወዲህ ከቀድሞው በተለየ በየዕለቱ በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ በመምጣት፤ በዛሬው ዕለት 915 የሚኾኑ አዳዲስ ተጠቂዎች መገኘታቸው ታወቀ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ሐሙስ ሐምሌ ፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. July 9, 2020)፦ የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ፕሬዝዳንት እስክንድር ነጋ እና አመራሮችን መታሰር ተከትሎ ፓርቲው ባወጣው መግለጫ፤ ሰሞኑን ጽንፈኞች በቀሰቀሱት አመጽ ለደረሰው እልቂትና ንብረት ውድመት የአንድ ቀን ጀንበር የወለደው ችግር አለመኾኑን ገለጸ። ፓርቲው የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት በአገሪቱ እየታየ ለሚገኘው ሥርዓት አልበኝነትና ሲልም ሽብርተኛነት ቀጥተኛ ተጠያቂዎች እንደሆኑ አበክሮ እንደሚያምን በመግለጫው አሳውቋል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ረቡዕ ሐምሌ ፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. July 8, 2020)፦ ለበርካቶች ሕይወት መጥፋት፣ መቁሰል፣ ግምቱ ለጊዜው ላልታወቀ በርካታ ንብረት መውደም ምክንያት ከኾነው ኹከት ጋር በተገናኘ ታዋቂ ሰዎች፣ የፖለቲካ አመራሮችና የመንግሥት ኃላፊዎች እየታሰሩ ይገኛሉ። የሻሸመኔ ከተማ ከንቲባ አቶ ተማም ሁሴን እና የከተማዋ አስተዳደርና የጸጥታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ናደው አምቦ ከተጠርጣሪዎቹ ውስጥ በመኾናቸው በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለጸ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ረቡዕ ሐምሌ ፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. July 8, 2020)፦ ባለፈው ሳምንት ሰኞ ምሽት ላይ የአርቲስት ሐጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ በኦሮሚያ፣ በአዲስ አበባ፣ በሐረርና ድሬዳዋ ተቀስቅሶ በነበረው ኹከት የተጠረጠሩና በቁጥጥር ሥር የዋሉ ሰዎች ቁጥር ከ4,700 በላይ መድረሱ ተነገረ። የሟቾች ቁጥር 167 መድረሱን የፌዴራል ፖሊስ ገለጸ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ማክሰኞ ሰኔ ፴ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. July 7, 2020)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ማክሰኞ ሰኔ 30 ቀን 2012 ዓ.ም. ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ጋር ተገናኝተው በበጀት ጉዳይ ላይ ማብራሪያ ይሰጣሉ። በወቅታዊ ጉዳዮችና የአርቲስት ሐጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ በተከሰተው ኹከት፣ የሰው ሕይወት መጥፋትና የንብረት ውድመት ጋር በተያያዘም ማብራሪያ እንደሚሰጡ ተገምቷል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ሰኞ ሰኔ ፳፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. July 6, 2020)፦ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ዛሬ ሰኞ ሰኔ 29 ቀን በሊቀመንበሩ በአቶ በለጠ ሞላ አማካኝነት በሰጠው መግለጫ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሕወሓት የሠጠውን የፓርቲ ምዝገባ ሰርቲፊኬት እንዲሰርዝ ጥያቄ አቀረበ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ሰኞ ሰኔ ፳፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. July 6, 2020)፦ ከአርቲስት ሐጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር ተያይዞ በተቀሰቀሰው ኹከትና የበርካቶችን ሕይወት ካጠፋው ጉዳይ ጋር ተያይዞ የትግራይ ቲቪ እና ድምፂ ወያኔ ከሳተላይት እንዲወርዱ መንግሥት ማድረጉ ታወቀ። በአገር ቤት ሥርጭታቸውን ለማቆም ተገድደዋል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (እሁድ ሰኔ ፳፰ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. July 5, 2020)፦ ኢትዮጵያ የህዳሴውን ግድብ ውኃ ለመሙላት የሚያስችላትን ግንባታ መጨረስዋንና የውኃ መሙላት ሒደቱን እንደምትጀምር የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢንጂንየር ስለሺ በቀለ ገለጹ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (እሁድ ሰኔ ፳፰ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. July 5, 2020)፦ የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ ዛሬ እሁድ ሰኔ 28 ቀን 2012 ዓ.ም. ወደ ግብጽ በመሔድ ከፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ ጋር ተገናኙ። በሁለቱ አገሮችና በአፍሪካ ቀንዱ በሚገኙ አጎራባች አገሮች ዙሪያ ይነጋገራሉ ተብሏል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...