እስክንድር ነጋ ታስረው ተፈቱ

Eskinder Nega

በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ቤታቸው የፈረሰባቸው ድሆችን ሲጎበኙ ነበር

ኢዛ (ቅዳሜ ሚያዝያ ፲፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 25, 2020)፦ የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፕሬዝዳንት አቶ እስክንድር ነጋ ዛሬ ጠዋት ቅዳሜ ሚያዝያ 17 ቀን በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የፓርቲው አመራሮች ገልጸዋል። ከምሽቱ ሦስት ሰዓት አካባቢ ተፈትተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የህዳሴ ግድብን የውኃ ሙሌት ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው

Grand Ethiopian renaissance dam

የግድቡ የብረታ ብረት ሥራ መቶ በመቶ መጠናቀቁ ተገለጸ

ኢዛ (ዓርብ ሚያዝያ ፲፮ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 24, 2020)፦ የህዳሴ ግድብን በሐምሌ ወር 2012 ዓ.ም. ውኃ ለመሙላት ቅድመ ዝግጅት እየተደረገና የግድቡ የብረታ ብረት ፍሬም ሥራ መቶ በመቶ መጠናቀቁን የታላቁ ህዳሴ ግንባታ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከኮሮና ቫይረስ ያገገሙ 25 ደረሱ

3ዲ (3D) ኮሮና ቫይረስ በምስል (© istock.com/Dr_Microbe)

ዛሬ አንድ የቫይረሱ ተጠቂ ተገኝቷል

ኢዛ (ዓርብ ሚያዝያ ፲፮ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 24, 2020)፦ በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ መጠቃታቸው ከታወቁ ሰዎች ውስጥ ማገገም የቻሉት 25 ደርሰዋል። ዛሬ አንድ በቫይረሱ የተጠቃ ሰው መገኘቱን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ2012 ዓ.ም. 32ኛ ሳምንት አንኳር ወሬዎች

Ethiopia Zare's weekly news digest, week 32nd, 2012 Ethiopian calendar

የዓመቱ ሠላሳ ሁለተኛ ሳምንት አንኳር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ክንውኖች

ኢዛ (ከሚያዝያ 5 - 11 ቀን 2012 ዓ.ም.)፦ ያሳለፍነው ሳምንት በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት ከሚከበሩት በዓላት መካከል አንዱ የኾነው የትንሣኤ በዓል የሚከበርበት የመጨረሻ ሳምንት የዋለበት ነው። በቀጣይ ሳምንት ደግሞ የታላቁ ረመዳን ጾም ይጀምራል። እነዚህ የሃይማኖት ተከታዮች በሕብረት ኾነው የሚያከብሩት ቢኾንም ዘንድሮ እንደቀደመው ጊዜ የሚከበሩ አይኾኑም። ከሰሞኑ የትንሣኤ በዓል ዋዜማ ላይ የተመለከትነው ይህንኑ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እርምጃዎች ጥቂቶቹ

በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉ አስጫሾችና አስቃሚዎች፤ እንዲሁም ዕቃዎቻቸውና ጫት

ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በመተላለፍ ሲሻ ሲያስጨሱና ጫት ሲያስቅሙ የነበሩ በቁጥጥር ስር ውለዋል

ኢዛ (ሐሙስ ሚያዝያ ፲፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 23, 2020)፦ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በማፃረሩ ተግባራት ላይ ተሰማርተው በሚገኙ ግለሰቦች ላይ እርምጃዎች እየተወሰዱ መኾኑን ሰሞኑን በተከታታይ የሚወጡ መረጃዎች እያመላከቱ ነው። ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በመተላለፍ ሲሻ ሲያስጨሱና ጫት ሲያስቅሙ የነበሩ በቁጥጥር ስር ውለዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአስቸኳይ ጊዜውን አዋጅ ጥሰው የሠረጉት ሕግ አስከባሪ በቁጥጥር ሥር ዋሉ

ፖሊስ

“ካልሰማህ ሕግ ተፈፃሚ ይኾንብሃል!”

ኢዛ (ሐሙስ ሚያዝያ ፲፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 23, 2020)፦ ይህ ዜና የተሰማው ከአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ዲማ ወረም ወረዳ ነው። ወቅታዊውን የኮሮና ቫይረስ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በመጣስ በተፈፀመ ሕግ መተላለፍ አንድ ሰው በቁጥጥር ሥር ውሎ መታሰሩን ያመለክታል። ሕግ ጥሷል ተብሎ በሕግ ጥላ ሥር የሚገኘው ሰው ደግሞ ሕግ አስከብር ተብሎ ኃላፊነት የተሠጠው ሰው ነው። ፖሊስ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገላቸው 10,736 ደርሰዋል

የጤና ሚኒስቴር

ባለፉት 24 ሰዓት 965 ተመርምረው ሁሉም ነፃ ኾነዋል

ኢዛ (ሐሙስ ሚያዝያ ፲፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 23, 2020)፦ በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ምርመራ መደረግ ከተጀመረበት ጊዜ ወዲህ በአጠቃላይ ምርመራ የተደረገላቸው ሰዎች ቁጥር ከ10 ሺሕ በላይ ሲደርስ ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ 965 ሰዎች ተመርምረው አንድም የቫይረሱ ተጠቂ ሳይገኝ ቀርቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ንግድን በማስተጓጐል እርምጃ የተወሰደባቸው ከ25 ሺሕ በላይ ደረሱ

አቶ መላኩ አለበል

420 ታስረዋል፤ 890 የንግድ ፍቃዳቸው ተሰርዟል፤ 13,500 የንግድ ድርጅቶች ታሽገዋል

ኢዛ (ረቡዕ ሚያዝያ ፲፬ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 22, 2020)፦ ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ የንግድ እንቅስቃሴውን አስተጓጉለዋል በሚል የተለያዩ እርምጃዎች የተወሰዱባቸው የንግድ ድርጅቶች ቁጥር ከ25 ሺሕ በላይ መድረሱ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ