ዶክተር ዐቢይ የሽግግር መንግሥት ይቋቋም የሚለውን ጥያቄ ውድቅ አደረጉ

PM Abiy Ahmed held a meeting with opposition party leader

ጥያቄውን የሽግግር ሳይሆን የብጥብጥብ ብለውታል

ኢዛ (ዓርብ ሚያዝያ ፳፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. May 1, 2020)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ “የሽግግር መንግሥት ይቋቋም” በሚል የሚቀርቡ ጥያቄዎችን፤ “የብጥብጥ መንግሥት ይቋቋም” እንደማለት እንደሚቆጥሩት ገልጸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አይ.ኤም.ኤፍ ኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል የምታውለው 411 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ሊሰጥ ነው

የዓለም የገንዘብ ድርጅት (IMF)

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ምስጋና አቀረቡ

ኢዛ (ዓርብ ሚያዝያ ፳፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. May 1, 2020)፦ ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይ.ኤም.ኤፍ) የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል ለሚደረገው ጥረት የሚውል የ411 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለኢትዮጵያ እንዲሰጥ የሚያስችለውን ውሳኔ አጸደቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በዛሬው መረጃ በሕክምና ላይ ከሚገኙት ተጠቂዎች ያገገሙት ቁጥር በልጧል

Total coronavirus cases in Ethiopia, 2020-05-01

በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተጠቁት ቁጥር 133 ደርሷል

ኢዛ (ዓርብ ሚያዝያ ፳፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. May 1, 2020)፦ የጤና ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው ሪፖርት በ24 ሰዓት የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ከተደረገላቸው 913 ሰዎች ውስጥ፤ ሁለቱ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ በመገኘታቸው፤ በኢትዮጵያ በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 133 መድረሱን ሲያመላክት፤ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ የኮሮና ቫይረስ ተይዘው ከነበሩት ታማሚዎች ውስጥ በሕክምና ላይ ከሚገኙት ይልቅ ያገገሙት ቁጥር በልጧል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዛሬ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በምርጫው መራዘም ላይ ይወያያል

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በተመለከተ ያቀረበውን የውሳኔ ሐሳብ ላይ ይመክራል

የምርጫውን ጉዳይ ጨምሮ አምስት አጀንዳዎችን ያጸድቃል ተብሏል

ኢዛ (ሐሙስ ሚያዝያ ፳፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 30, 2020)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስድስተኛውን አገራዊ ምርጫ ለማካሔድ የሚያስችል ሁኔታ ባለመኖሩ፤ ምርጫ 2012 በሰሌዳው መሠረት ምርጫውን ነኀሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም. ለማካሔድ እንደማይችል ባቀረበው የውሳኔ ሐሳብ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ መርምሮ ያጸድቃል ተብሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ራስዋን ንግሥተ ነገሥት ዘኢትዮጵያ በሚል የምትጠራዋን ግለሰብ ፖሊስ አሰራት

እኅተ ማርያም

60 ደላሎች ታስረዋል

ኢዛ (ረቡዕ ሚያዝያ ፳፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 29, 2020)፦ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ራስዋን “ንግሥተ ነገሥት ዘኢትዮጵያ” የሚል መጠሪያ በመስጠት ስትንቀሳቀስ የቆየችው እኅተ ማርያም በሚል መጠሪያ የምትታወቀው ግለሰብ ዛሬ ከመሸ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መንግሥት በምርጫ ጉዳይ አራት አማራጮችን በማቅረብ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር እየመከረ ነው

PM Abiy Ahmed

ሲቪክ ማኅበራትም በውይይቱ ተሳትፈዋል

ኢዛ (ረቡዕ ሚያዝያ ፳፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 29, 2020)፦ በኮሮና ወረርሽኝ ሳቢያ የተራዘመውን ስድስተኛውን አገራዊ ምርጫን (ምርጫ 2012) ለማካሔድ አስቸጋሪ በመኾኑ፤ መንግሥት አራት የመፍትሔ ሐሳቦችን በማቅረብ ከተፎካካሪ ፓርቲዎችና ሲቪክ ማኅበራት ጋር ውይይት በማካሔድ ላይ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አብን የሕገ መንግሥቱ ማሻሻያ ጊዜው አሁን ነው አለ

National Movement of Amhara (NAMA)

ጊዜያዊ መንግሥት እንዲመሠረትም ጥሪ አቅርቧል

ኢዛ (ረቡዕ ሚያዝያ ፳፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 29, 2020)፦ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ጊዜው አሁን መኾኑንና ብሔራዊ የአንድነትና ጊዜያዊ መንግሥት ማቋቋም እንደሚገባ ጥሪ ያስተላለፈበትን መግለጫ ዛሬ ረቡዕ ሚያዝያ 21 ቀን 2012 ዓ.ም. አውጥቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ2012 ዓ.ም. 33ኛ ሳምንት አንኳር ወሬዎች

Ethiopia Zare's weekly news digest, week 33rd, 2012 Ethiopian calendar

የዓመቱ ሠላሳ ሦስተኛ ሳምንት አንኳር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ክንውኖች

ኢዛ (ከሚያዝያ 12 - 18 ቀን 2012 ዓ.ም.)፦ ያሳለፍነው ሳምንት ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ዜናዎች ባሻገር ሌሎች ክንውኖች የሚመለከቱ የተለያዩ ዜናዎች ብቅ ያሉበት ነው ማለት ይቻላል። ከእነዚህ ውስጥ በዓባይ ተፋሰስ አገሮች አወዛጋቢ የኾነው የህዳሴ የውኃ ሙሌት መርኀ ግብርን በተመለከተ ኢትዮጵያ በአቋሟ መጽናትዋን ያረጋገጠችበትን የውኃ ሙሌት ሥራውን ለማድረግ ዝግጅት መጀመሯንና የግድቡ ሥራ ተጠናክሮ ስለመቀጠሉ ያሳወቀችበት መረጃ ተጠቃሽ ነው። በመጪው ክረምት አምስት ቢሊዮን ችግኝ ለመትከል የታቀደውንም ከግብ ለማድረስ እየተሠራ መኾኑንና ለዚሁ የሚኾነውን ችግኝ ልማት ያለበትን ሁኔታን የሚያሳይ የመስክ ጉብኝት መደረጉም ሌላው ተጠቃሽ ጉዳይ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ተይዘው ያገገሙት 50 ደርሰዋል

Total coronavirus cases in Ethiopia, 2020-04-27

በዛሬው ሪፖርት 933 ሰዎች ተመርምረው፤ አንድ በቫይረሱ የተጠቃ ተገኝቷል

ኢዛ (ሰኞ ሚያዝያ ፲፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 27, 2020)፦ በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ሪፖርት ከተደረጉትና በለይቶ ሕክምና መስጫ ማዕከል ከሚገኙት ታማሚዎች ውስጥ ማገገም የቻሉት 50 ደርሰዋል። አንድ ሰው በቫይረሱ የተጠቃ ተገኝቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሼህ ሙሐመድ አል-አሙዲ የቀኝ እጅ የሚባሉት ዶ/ር አረጋ ኃላፊነታቸውን ለቀቁ

ሼህ ሙሐመድ ሑሴን አል-አሙዲ (በግራ)፤ ዶ/ር አረጋ ይርዳው (በቀኝ)

ለሜድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ጊዜያዊ ሥራ አስፈጻሚ ተሰየመ
ከሥራ መልቀቃቸው ደባዎች በመደራረባቸው ነው ተብሏል

ኢዛ (ሰኞ ሚያዝያ ፲፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 27, 2020)፦ በኢትዮጵያ ውስጥ ከፍተኛ መዋለ ነዋይ በማፍሰስ የሚታወቀውንና በስሩ ወደ 27 የሚኾኑ ኩባንያዎች ያሉትን ሜድሮክ ኢትዮጵያን በመምራት የሚታወቁትና የሼህ መሐመድ አላሙዲን የቅርበ ወዳጅ ዶክተር አረጋ ይርዳው ኃላፊነታቸውን ለቀቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ