መሪውን ያላስፈታ ፓርቲ አዝማች እንደሌለው ጦር ይቆጠራል

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ስሜነህ ታምራት (ከስዊድን)

"... ገዢው መንግሥት ሥልጣን ሲለቅ ተቀናቃኝ የነበሩ የፖለቲካ እስረኞች እንደሚፈቱማ ማንም የሚያውቀውና ባለፉት ሁለት መንግሥታት መለዋወጥም አይተነዋል። አሳሪውን መንግሥት በምርጫ ከሥልጣን ስናስወግደው ያኔ የብርቱካን ነፃነትም ይከበራል ብሎ መናገር ወያኔ እስከሚወርድ ድረስ ብርቱካን በእስር የመቆየቷን ጉዳይ አምኖ እንደመቀበልም ይቆጠራል። ከዚህም ባሻገር የዕድሜ ልክ እስራቱንም ቢሆን እንደመቀበል ይመስላል። ይህ መግለጫ በተለይ ከራሷ ፓርቲ አንደበት መውጣቱ በእጅጉ ያሳፍራል። ..."

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ካለፉ ትብብሮች - ለትምህረት (አሸብር)

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

አሸብር (ከጀርመን)

“እርስ በርሳችሁ ስትተራመሱ የወያኔን አንድ ዝንብ እንኳን ‘እሽ‘ ሳትሉ ዕድሜአችሁን ገፋችሁ“ ከታዛቢ

በአሁኑ ጊዜ የተለያዩ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ድርጀቶች ስለሕብረት ጉዳይ ሲወያዩ፤ አልፎ - አልፎ የሚያነሱት ጉዳይ ካለፉት ትብብሮች ምን መማር እንዳለባቸው ነው። ስለሆነም ካለፉ ትብብሮች ሊገኝ ስለሚችል ትምህርት አጋጣሚ ያስገኘልኝን ግንዛቤ ባካፍል በጥቂቱም ቢሆን አስተዋጽዖ ይኖረዋል ብዬ ስለገመትኩ የምትከተለዋን ለማለት ሞክሬአለሁ። በቅድሚያ ግን አንባቢዎችን ማሳሰብ የምሻው፤ የጽሑፌ ዓላማ በየጊዜው የተቋቋሙ ሕብረቶች ውስጥ በእኔ ዕይታ ለጋራ ትግሉ እንቅፋቶች ነበሩ ያልኳቸውን ድርጊቶች ለማሳየትና ለወደፊት ትምህርት የሚቀሰምባቸው ይሆናሉ በሚል ብቻ እንጂ፤ ባለፉት ለተፈጸሙ ልማቶችም ሆኑ ጥፋቶች ማንንም ተጠያቂ አድርጎ ለማቅረብ የታሰበ እንዳልሆነ ነው። ስለዚህም በጽሑፌ ውስት በክፉም ሆነ በደግ የማንንም ግለሰብ ሆነ ድርጅት ስም አላነሳሁም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መድረክ ሊደገፍ ይገባዋል - ኢትዮጵያዊነትን ያንጸባረቀ ነውና (አማኑኤል ዘሠላም)

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

አማኑኤል ዘሠላም This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

ከሦስት ዓመት በፊት ወደነበረው የሀገራችን የፖለቲካ ሁኔታ ለትውስታ ያህል ልመልሳችሁ። ተቀማጭነታቸው አሜሪካን ሀገር የሆኑ፣ የቀድሞ የሰሜን አሜሪካ የቅንጅት ድጋፍ ማኅበር ጥቂት አመራር አባላት፣ በሆላንድ ሀገር ከኦሮሞ ነፃ አውጭ ግንባር፣ ከኦጋዴን ነፃ አውጭ ግንባር፣ ከኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር እና ከሲዳማ ህዝብ ነፃ አውጭ ግንባር ጋር ትብብር ለነፃነትና ለዲሞክራሲ (ኤ.ኤፍ.ዲ.) የሚባል አካል መሰረቱ። ይህ አካል በተለይም በውጭ ሀገር ትልቅ መከፋፈልን ፈጥሮ እንደነበረ ይታወሳል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከቫንኩቨር እስከ ዳላስ: ከግንቦት ሰባት እስከ ግንቦት ሀያ

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

 

ልጅ ተክሌ
የጳውሎስ  ማላገጥ፡ የመረራና ብሬ ቁጣ

ሕወሀት ከደርግ አምባገነን አገዛዝ ነጻ ባወጣን (ተረጋጉ፡ አልጨረስኩም)፡ እንደገና ግን ወደ ሕወሀት ቀጣይ የባሰ አምባገነንና ዘረኛ ስርአት በተሸጋገርን ባስራ ስምነተኛው ዓመት፡ ዳላስ፡ ቴክሳስ ውስጥ፡ ከዶ/ር ብርሀኑ ፊትና ጎን ተቀምጠናል። ታሪክ ማጠንጠን ጀመርን።


ሙሉውን አስነብበኝ ...

ክርስትና እና ፖለቲካ (ግርማ ካሣ)

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

ግርማ ካሣ

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ!

(ይህ መልዕክት የክርስትና እምነት ተከታይ ለሆኑ ኢትዮጵያውያን የተዘጋጀ ነው። ነገር ግን ጌታችን መድኃኒታች ኢየሱስ ክርስቶስ በሙስሊሞች ዘንድም ኢሣ ተብሎ እንደ ታላቅ ነብይ የሚቆጠር ስለሆነ፣ ለሙስሊም ወገኖቼም በተዘዋዋሪ መንገድ ትምህርት ሰጪ ነው ብዬ አስባለሁ።)

የአትላንታ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መጋቢ የሁኑት ቄስ ቶሎሳ ጉዲና ንግግር ያደረጉበት አንድ ታላቅ መንፈሣዊ ስብሰባ በአዲስ አበባ ታላቁ ስቴዲየም ተደርጎ እንደነበረ ሰምቻለሁ። ከስታዲየሙ ትንሽ ሄድ ብሎ በሚገኘው በመስቀል አደባባይ፣ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ወገኖቻችን በተገኙበት፣ የመስቀል በዓልን ምክንያት በማድረግም ከጥቂት ቀናት በፊት፣ አቡነ ፓትሪያክ ጳውሎስ ንግግር አድርገው ቡራኬ ሰጥተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በሲያትል ተደመምን፤ በካልግሪም ኮራን፤ በፖርትላንድም ተደነቅን

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

አለቃ ተክሌ - ከቫንኩቨር

ሀተታ እና አስተያየት፤ ከቫንኩቨር ንግስ መልስ ወደ ፒስ (ፒትስ) በ(ር)ግ

ሊቀ ዲያቆኑ፤ የሲያትል ህዝብ

ሊቀ ዲያቆን ታደሰ የሲያትሉ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ዲያቆን “ቲኬት ግዙ ምናምን አትበሉን። ትኬታችሁን ያዙ። በእለቱ ብቻ ተዘጋጅታችሁ ጠብቁን” ብሎ ለሲያትል ህዝብ ልንቸበችብ የወሰድነውን ቲኬት ሲመልስብን ትንሽ ደንግጠን ነበር። የበአሉ ጊዜ እያነሰና እያጠረ ደግሞ እየቀነሰ ሲመጣ ሰው ይመጣ ይሆን ብለን ትንሽ ማሰባችን፤ ትንሽም መጠራጠራችን አልቀረም። ልበ ሙሉው ሊቀ ዲያቆን ግን ይገስጸን ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...