መሪውን ያላስፈታ ፓርቲ አዝማች እንደሌለው ጦር ይቆጠራል
ስሜነህ ታምራት (ከስዊድን)
"... ገዢው መንግሥት ሥልጣን ሲለቅ ተቀናቃኝ የነበሩ የፖለቲካ እስረኞች እንደሚፈቱማ ማንም የሚያውቀውና ባለፉት ሁለት መንግሥታት መለዋወጥም አይተነዋል። አሳሪውን መንግሥት በምርጫ ከሥልጣን ስናስወግደው ያኔ የብርቱካን ነፃነትም ይከበራል ብሎ መናገር ወያኔ እስከሚወርድ ድረስ ብርቱካን በእስር የመቆየቷን ጉዳይ አምኖ እንደመቀበልም ይቆጠራል። ከዚህም ባሻገር የዕድሜ ልክ እስራቱንም ቢሆን እንደመቀበል ይመስላል። ይህ መግለጫ በተለይ ከራሷ ፓርቲ አንደበት መውጣቱ በእጅጉ ያሳፍራል። ..."





