ነፍስና ስጋ፤ ትናንት ለስጋችን ነበር ዛሬ ደግሞ ለነፍሳችን

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

አለቃ ተክሌ

እነሆ ቅድስት ማርያም በቫንኩቨር ልትከብር ነው

ሰንጋው ተመርጧል፤ ቢላ ተስሏል

ሰንጋው ተመርጧ። ጋሽ ከቤና ሙሌ ናቸው የመረጡት። ጋሽ ከቤ ባለፈው ወደ ዲሲ ለመስከረም 3ቱ ሰልፍ ሊያመራ ሲያኮበኩብ የነበረው ከበደ ሀይለማሪያም ነው። እህቶቻችንና እናቶቻችን እኛን ወንዶቹን ወደምድጃ አናስደርስም ብለው ወገባቸውን አስረው ተነስተዋል። እዚህ ከምእራቡ ዓለም ሁላችንም ጾታችን አንድ እንደሆነ አላወቁም። ወይ ሁላችንም ሴቶች ነን። ወይም ሁላችንም ወንዶች ነን።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እኛና ጠላት፣ ሰልፍና ሰይፍ፤ ሰይፍ አልመዘዝንም እስኪ ሰልፍ እንውጣ፤ ሴፕቴምበር 13፣ 2009

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

አለቃ ተክሌ - ቫንኩቨር ካናዳ

ይሄ ፅሁፍ የቅስቀሳ ነው፤ ከጋሽ ከቤ ልጀምር

ቅስቀሳ የማይወድ ከዚህ ሳይዘልቅ ያቁም። ብዙ አይልፋ። እነሆ ቅስቀሳ። አሁን ጥቅምት ሲመጣ 56ኛ ዓመቱን ይይዛል። ያሳዝነኛል። አንዳንደዬ ቢያናድደኝም፤ ሁልግዜ ግን ያስደስተኛል። ከቫንኩቨር ሲያትል ከሲያትል ዲሲ፡ ከዲሲ ቶሮንቶ ከቶሮንቶ ደግሞ መልሶ ካልግሪ ሲንከራተት፡ ጽናቱ ይገርመኛል። ፅድቅን ፍለጋ አይደለም። ሰማያዊ ድህነትን ሽቶም አይደለም። ዝናና ክብርም አይደለም ረሀቡ። የኢትዮጵያ ጉዳይ እያንገበገበው እንጂ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በእውኑ እኛ ከብርቱካን ምን አለን? ብርቱካንስ ከኛ ምን አላት?

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

አለቃ ተክሌ (ለዓመቱ ታላቅ ሰው ሽልማት ሥነሥርዓት ላይ ቀረበ)

የብርቱ ካህን ፈተናና የብርቱ ካህን የሕይወት ጥሪ

ደሳሳ ጎጆ። ፍቅር። በእበት የተለቀለቀ ወለል። አርበጠባብ አልጋዎች። የልጅ እናት። ብርቱካን፡ ቀድሞውንም፡ በልጅነቷ ካህን እንድትሆን የተጠራች መሆኗና መናገር ይቻላል። የታመሙትን ለማጥናናት፡ የተበደሉትን ለመካስ፡ የተጠቁትን ለመከላከል፡ ተስፋ ያጡትን ተስፋ ለመመገብ፡ ፍትህ ያጡትን ደግሞ ፍትህ ለማደል፡ የተጠራች ካህን። የዛሬ ሶስት ሳምንት አካባባ፡ ዋሽንግተን ዲ.ሲ. ያገኘሁት ሳምሶን ጋዜጠኛ ነው። ወይም ነበር። እኔና ሳምሶን፡ የኬንያን ስደት ለሶስት ዓመታት ባንድ ላይ አርሰነዋል። ገፍተነዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መኢአድና አንድነት እንዲዋሃዱ የቀረበ ጥሪ (አማኑዔል ዘሠላም)

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

አማኑዔል ዘሠላም ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. ) ነሐሴ 29 ቀን 2001 ዓ.ም.

“መሪያችን ብርቱካን ሚደቅሳ በግፍ ታስራ፣ ደጋፊዎቻችን በየቦታው ወከባ እየደረሰባቸው፣ በህዝብ ገንዘብ የሚተዳደሩ የመንግሥት መገናኛ ብዙኀን ርካሽ ፕሮፖጋንዳ እየረጩ፣ ስለምርጫ ማሰብና ስለ ምርጫ ማውራት እራስን ማታለል ነው። አንዳች ጥቅም ለማያመጣ ገዢው ፓርቲ በውጭ ሀገር መንግሥታት ለመደገፍ ሲል ብቻ የሚጫወተውን የፖለቲካ ጨዋታ ለማዳመቅ ፍላጎቱ የለንም።” [1]

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለመስከረም 3 ሰልፍ ጋባዣችን ህሊናችን ነው (ፍቅሩ ይበልጣል)

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

ፍቅሩ ይበልጣል

መስከረም 3 ቀን 2002 ዓ.ም. (September 13, 2009) በዋሽንግተን ዲ.ሲ. በዋይት ሐውስ ፊት ለፊት 100 ሺህ ዕድምተኛ የሚጠበቅበት እና ወያኔ በህዝባችን ላይ የፈጸማቸውንና በመፈፀም ላይ ያለውን በደል፣ ስቃይ፣ ግድያና እስራት ለማጋለጥ ኢትዮጵያውያንና ሌሎችም ኢትዮጵያንና ህዝቧን የሚወዱ ሁሉ ሊገኙበት የሚገባ ታላቅ ሰልፍ የሚደረግበት ቀን ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሠላማዊ ትግል ሐዋርያው አቶ ስየ አብርሃ (ሄለን ነገራ)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ሄለን ነገራ This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. 

ሰሞኑን በአዳማ ከተማ የአንድነት ፓርቲ የጠራው ስብሰባ በድንኳን ሰባሪዎች ተገለበጠ ተብሎ የተለያዩ አስተያቶችን እያነበብን ነው። እውነቱን ለመናገር ለኔም ሆነ ለጓደኞቼ ምንም የሚደንቅም የሚያናድድም ዜና አልነበረም። ወያኔም ያንን አስመልክቶ በአቶ በረከት ስምዖን በኩል የተለመደ የውሸት ማስተባበያውን መስጠቱም አልደነቀኝም። ይልቁንም እኔን የገረመኝ ያንን ክስተት አስታከው የቀድሞ የወያኔ ቁንጮ ባለሥልጣን አቶ ስየ አብርሃ የሰጡት መግለጫ (ጽሑፍ) ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...