በሳውዲ ዐረቢያ የኢትዮጵያውያን መከራ (ክፍል አንድ)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

በሳውዲ ዐረቢያ የምንገኝ ግፉአን ኢትዮጵያውያን መከራ - በረመዳን ዋዜማ (ክፍል አንድ)

ነቢዩ ሲራክ - ከሳውዲ ዐረቢያ

... በመቶዎች የሚቆጠሩ የመናውያን፣ ኢትዮጵያውያን፣ ሶማሌያውያንና ኤርትራውያን ስደተኞች አደገኛውን የቀይ ባህር በትናንሽ ጀልባዎች ታጭቀው የጨካኝ አሸጋጋሪ ደላሎችን ግፍ የተሞላበት እርምጃ በመቋቋም የማይጨበጠውን ህልምን ለማሳካት ትግል ይዘዋል። አብዛኛው ወንዶች እየተደበደቡ ሴቶች እየተደፈሩ የየመንን በርሃዎች ቆርጠው ወርቅ ይታፈሳል ወደ ተባለበት የቱጃሮች ሀገር ሳውዲ ዐረቢያ ሲገቡ ይያዛሉ። ለወህኒ ከማዳረግ አልፎ በጥይት እየተደበደቡ ደመ-ከልብ ይሆናሉ። ጥቂት የቀናቸው አይሆኑ ሆነው ካሰቡት ሲደርሱ ያላለላቸው በርሃ በልቶዋቸው የመቅረቱን ትኩስ ዜና ሰምተን ሳናጣጥመው ሌላ ህሊና ሊቀበለው በማይችል ዜና መስማት ጀምረናል። በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በሳውዲ የጠረፍ ከተማ በጀዛን ድንበር ከተያዙ በኋላ በተጨናነቀው እስር ቤት አሳር መከራ እያዩ መሆናቸውን እንሰማለን። ይህንን ከተለያዩ ምንጮችና ከሰብዓዊ መብት ተከራካሪዎች ማረጋገጥ ቢቻልም ሁኔታውን አሳምረው ከሚያውቁት ከመንግሥታቸን ተወካይ ባለስልጣናት ግን ማረጋገጫ ማግኘት አልተቻለም። ይህ በእንጥልጥል ላይ እንዳለ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በበኩላቸው በጂዳ የግርድና አስከፊ ኑሮ አንገፍግፏቸው ወደ ሀገራቸው የሚመልሳቸው አጥተው ለወራት በእንግልት ላይ መሆናቸውን ሰማሁ። ...

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሦስተኛው መድፍ

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

ተስፋዬ ገብረአብ

እነሆ! “የስደተኛው ማስታወሻ” የተባለው መድፍ ተሠርቶ ተገባዶአል …

በዚህ አያያዜ ቶሎ የምጨርሰው ይመስለኛል። “ስደት” ርዕሰ ጉዳዩ ሰፊ ነው። ይፃፍ ከተባለ 20 ጥራዝም አይበቃው። ሆኖም አጀንዳዬ ከሀገራችን ፖለቲካ ሊያፈነግጥ እንደማይችል ግልፅ ነው። የአብዛኛው የስደት ምክንያቱ ፖለቲካውም አይደል? በመሆኑም ስደትና ፖለቲካውን ከወቅታዊ ጉዳዮቻችን ጋር እያዋሃድኩ እተርካለሁ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ነብይ በአገሩ አይከበርም” … እውነት!? (ማስተዋል አዳነ)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ክፍል አንድ (ማስተዋል አዳነ)

ጊዜው በአገራችን ክረምት ሊገባ ጥቂት ጊዜያት የቀሩበት ወቅት ነበር፤ የአሁኑ ክረምት። ወደአገር ቤት ለመሄድ የወሰንኩት ቤተሰብ፣ ጓደኛና ዘመድ ለመጠየቅና በአጠቃላይ የአገራችን የኑሮ ሁኔታ በጣም ስለናፈቀኝ፤ ይህንን ደግሞ ከተወሰነ አመት የትምህርት ቆይታ በኋላ ተመልሼ ማየት አለብኝ የሚል ውሳኔ ላይ ስለደረስኩ ነበር። ተማሪ ስለሆንኩና የእረፍት ጊዜዬንም በዚሁ አጋጣሚውን መጠቀሙ ጥሩ አማራጭ ስለሆነ ከፍራንክፈርት ወደአዲስ አበባ ትኬት ቆርጬ ግንቦት መጨረሻ ላይ ወደአገር ቤት ለመሄድ ተሰናዳሁ። የበረራ ቀን ሰኞ ነበር። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከምርጫው በስተጀርባ - አንዳንድ ነጥቦች (ተስፋዬ ገብረአብ)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ተስፋዬ ገብረአብ

(አንዲት ቁራጭ “ወግ” ይዣለሁና እንደ መለስ ዜናዊ ቅንድባችሁን አሳምራችሁአንብቡኝ። “ጠቢቡ ሰለሞን” ለመሪያችን እንዳቀነቀነለት፣ “ውበት ቅንድቡ ላይ የፈሰሰለት - እውቀት ወደ አንጎሉ የዘለቀለት!” ተባለ። አልን! አስባልን! ይባላል! በምርጫው ዋዜማ አንድ ጓደኛዬ ዘንድ ቤቱ ሄጄ ሳለ፣ ሙሉውን አስነብበኝ ...