በሳውዲ ዐረቢያ የኢትዮጵያውያን መከራ (ክፍል አንድ)
በሳውዲ ዐረቢያ የምንገኝ ግፉአን ኢትዮጵያውያን መከራ - በረመዳን ዋዜማ (ክፍል አንድ)
ነቢዩ ሲራክ - ከሳውዲ ዐረቢያ
... በመቶዎች የሚቆጠሩ የመናውያን፣ ኢትዮጵያውያን፣ ሶማሌያውያንና ኤርትራውያን ስደተኞች አደገኛውን የቀይ ባህር በትናንሽ ጀልባዎች ታጭቀው የጨካኝ አሸጋጋሪ ደላሎችን ግፍ የተሞላበት እርምጃ በመቋቋም የማይጨበጠውን ህልምን ለማሳካት ትግል ይዘዋል። አብዛኛው ወንዶች እየተደበደቡ ሴቶች እየተደፈሩ የየመንን በርሃዎች ቆርጠው ወርቅ ይታፈሳል ወደ ተባለበት የቱጃሮች ሀገር ሳውዲ ዐረቢያ ሲገቡ ይያዛሉ። ለወህኒ ከማዳረግ አልፎ በጥይት እየተደበደቡ ደመ-ከልብ ይሆናሉ። ጥቂት የቀናቸው አይሆኑ ሆነው ካሰቡት ሲደርሱ ያላለላቸው በርሃ በልቶዋቸው የመቅረቱን ትኩስ ዜና ሰምተን ሳናጣጥመው ሌላ ህሊና ሊቀበለው በማይችል ዜና መስማት ጀምረናል። በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በሳውዲ የጠረፍ ከተማ በጀዛን ድንበር ከተያዙ በኋላ በተጨናነቀው እስር ቤት አሳር መከራ እያዩ መሆናቸውን እንሰማለን። ይህንን ከተለያዩ ምንጮችና ከሰብዓዊ መብት ተከራካሪዎች ማረጋገጥ ቢቻልም ሁኔታውን አሳምረው ከሚያውቁት ከመንግሥታቸን ተወካይ ባለስልጣናት ግን ማረጋገጫ ማግኘት አልተቻለም። ይህ በእንጥልጥል ላይ እንዳለ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በበኩላቸው በጂዳ የግርድና አስከፊ ኑሮ አንገፍግፏቸው ወደ ሀገራቸው የሚመልሳቸው አጥተው ለወራት በእንግልት ላይ መሆናቸውን ሰማሁ። ...
ሙሉውን አስነብበኝ ...




