“ሰውዬው ጉዴን አፈላው አይደል?” - በፈቃዱ ሞረዳ
ከበፈቃዱ ሞረዳ
“የጋዜጠኛው ማስታወሻ” በሚል ስያሜ አንድ መጽሐፍ አዘጋጅቶ (ጽፎ) በተለይም የ“ዲያስፖራው” ቡና ማጣጫና ወግ መሰልቀጫ ሆኖ የሰነበተው ተስፋዬ ገብረአብ በአንድ ድረ ገጽ ላይ ቃል ተውሶ፣ ስሜን ጠቅሶ ውንጀላ ቃጥቶ ነበር።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ከበፈቃዱ ሞረዳ
“የጋዜጠኛው ማስታወሻ” በሚል ስያሜ አንድ መጽሐፍ አዘጋጅቶ (ጽፎ) በተለይም የ“ዲያስፖራው” ቡና ማጣጫና ወግ መሰልቀጫ ሆኖ የሰነበተው ተስፋዬ ገብረአብ በአንድ ድረ ገጽ ላይ ቃል ተውሶ፣ ስሜን ጠቅሶ ውንጀላ ቃጥቶ ነበር።
ሙሉውን አስነብበኝ ...ልዑልሰገድ (ከአቢሲኒያ) This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.
የዛሬ 18 ዓመት ግንቦት 13 ረቡዕ አዲስ አበባ ውስጥ ዕኩለ ቀን ላይ በውይይት ታክሲ እጓዛለሁ። ከቀበና አቅጣጫ የአራት ኪሎ አደባባይን አቋርጦ ታክሲው ወደ ፒያሣ አቅጣጫ ይገሰግሳል። በታክሲው ስፒከር የዕለቱ የዜና ዕወጃ ይሰማል። ዜናው ከወትሮው የተለየ ነበር። ኮ/ል መንግሥቱ ሀገር ጥለው ኮበለሉ የሚል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን መንበረ ፕትርክና 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል አከባበር በቤተክህነቱ ግቢ
ምጥው ለቤ This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.
ሰኞ ሰኔ 29 ቀን 2001 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አስቸኳይ ምልዐተ ጉባዔ በመጥራቷ፤ ኃላፊነት ያለባቸው ሊቃነ ጳጳሳት በጉባዔው ላይ ለመሳተፍ ከየሀገረ ስብከታቸው ወደ መንበረ ፓትርያርኩ የእየተሰቡ መገኘታቸው ተደምጧል። ጉባዔው በቤተክህነቷ አካባቢ አለ ለሚባለው አስተዳደራዊ ችግር መፍትሔ ይሰጣል ተብሎ ይገመታል። ይህ ጉባዔ የሚካሄደው ቤተክህነቷ የራሷን ፓትርያርክ በሾመችበት በ50ኛ ዓመት ላይ ነው። ታሪክን አጣቅሶና ጉባዔውን አስመልክቶና “ምጥው ለቤ” የሚከተለውን ጽሑፍ አድርሶናል። መልካም ንባብ!
ሙሉውን አስነብበኝ ...ስለሺ ዘእንግልጣር This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.
“የምንታገለው ለመንደር ወይስ ለሀገር? መታገል ያለብን ለሀገር አነድነት ነው፣ ሀገር ከሌለች መንደር አይኖርምና።”
አቶ ኦባንግ ሜቶ ‘የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የትብብር ንቅናቄ’ መስራች ከተናገሩት ተተርጉሞ የተወሰደ
አተኩሮ ላየው ቅንነቱን ለመረዳት ጊዜም አይፈጅም። በተኮላተፈና ጥርት ባለ አማርኛውም ሆነ አቀላጥፎ በሚናገረው እንግሊዝኛው በጨዋ ኢትዮጵያዊነት ከአፉ የሚወጡት ቃላት ልብ ውስጥ ጠልቀው ይገባሉ። ዘወትር በሄደበት ሁሉ የሚናገረው ኢትዮጵያዊነትን ነው። ሊነግረን የሚፈልገው ልዩነታችንን ወደጎን በመተው እርስ በርሳችን በመነጋገር ችግሮቻችንን እየፈታን አንድነታችንን ማጠንከር እንዳለብን ነው። በዘርና በመሳሰሉት ዛሬ ገዥው ፓርቲ የሚያራምደው የጎሣ ፖለቲካ ውስጥ ገብተን በመዳከር እርስ በርሳችን እንዳንጠላላና እንዳንቀያየም ይማጸነናል። “የነገዪቱ ኢትዮጵያ እጣ ያሰጋኛል፤ ዛሬ ካልተባበርን፣ ኢትዮጵያዊ ነን የምንል ሁሉ እጅ ለእጅ ተያይዘን መሔድ ካልቻልን፣ ነፃና ፍትሕ የሰፈነባት ዲሞክራሲያዊ ኢትዮጵያን ለማየት የምንጓጓበትን ጊዜ ያርቅብናል እንጂ አያቀርብልንም” ይለናል ኦባንግ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...ግርማ ካሣ ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. ) ሰኔ 17 ቀን 2001 ዓ.ም.
ኢትዮጵያን በጽጌረዳ አበባ እመስላታለሁ። ጽጌረዳ አበባ በጣም ተወዳጅ የሆነች አበባ ናት። ብዙ ጊዜ በማስቀመጫ ውስጥ ተደርጋ የሚመጡ እንግዶች በሚያዩዋት ቦታ ትቀመጣለች። የክብር፣ የፍቅርና የውበት ምልክት ናት። ኢትዮጵያ ሀገራችንም በነፃነቷና በአንድነቷ ታፍራና ተክብራ የኖረች፣ ከተለያዩ ብሔረሰቦች የተውጣጡ ልጆቿ ውበቷ የሆኑላት፣ ለኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ለጥቁር ህዝብ ሁሉ ኩራት የሆነች ሀገር ናት።
ሙሉውን አስነብበኝ ...ግርማ ካሣ ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. )
ቶርቸር (ሰቆቃ) ከዓለም እንዲጠፋ የሚታገል የዓለም አቀፍ የፀረ-ቶርቸርና የተጎጂዎች ደጋፊ ድርጅት፣ የአዕምሮን ቶርቸር ሲተነትን፣ ረዘም ላለ ጊዜ በጨለማ ቤት ውስጥ ማስቀመጥን፣ እንቅልፍ ማሳጣትን፣ መድፈርንና የመሳሰሉትን ከቶርቸር ውስጥ ያስገባቸዋል። በእንደዚህ አይነት የአዕምሮ ቶርቸር የሚያልፉ ሰዎች እራሳቸውን እንዲጠሉ የሚያደርግና የሚቆይ ከፍተኛ የአዕምሮ በሽታን እንደሚያመጣ ይናገራሉ።[1]
ሙሉውን አስነብበኝ ...ኩችዬ ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. )
“ላም እሳት ወለደችና እንዳትልሰው እሳት፣ እንዳትተው ልጇ ሆነ!” - አበው
ይህ አባባል ግለሰቦችም ማኅበረሰቦችም በኑሮ ሂደት ውስጥ አስጨናቂ ምርጫ እንዲያደርጉ የሚገደዱባቸው ሁኔታዎች መኖራቸውን የሚያመለክት ነው። እነዚህ ሁኔታዎች ብንዘጋቸው የማይዘጉ፤ መልስ እስካላገኙ ድረስ ከፊታችን ዞር የማይሉ ችኰ ነገሮች ናቸው። 3ኛው የግልገል ግቤ ፕሮጀክት እንዲህ ሆኖብን ስለከረመ እንደልማዴ የማውቀውንና የሚሰማኝን ላካፍላችሁ መረጥሁ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...ወርቀ አማኑኤል ዘሰላም ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. )
ከሀገሬ ተሰድጄ የስደት ኑሮ ከጀመርኩኝ በርካታ ዓመታት አለፉ። አዲስ አበባ የነበርኩ ጊዜ የግል ትምህርት ቤት ስለተማርኩ እንግሊዘኛ ብዙ አይችግረኝም። ከፈረንጆች ጋር በኢትዮጵያዊ አነጋገር (accent) ደህና እግባባለሁ። ነገር ግን እንደ አማርኛ የውስጤን ሃሳብ መናገር አልችልም።
ሙሉውን አስነብበኝ ...ልዑልሰገድ (ከአቢሲኒያ) This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.
አዲስ አበባ ስታዲየም በተመልካች ግጥም ብሏል። ታዳሚው ገና ኳስ ጨዋታው ሳይጀመር ከየአቅጣጫው ድጋፉን ይገልጻል። በአቶ መለስ ጥብቅ ትዕዛዝ የተሰጣቸው ወታደሮች ከወትሮው በቁጥር ጨምረዋል። በጊዜው ጨዋታው በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና ከእናት ሀገሯ በተገነጠለችው ኤርትራ ቡድን መካከል የሚደረግ የወዳጅነት ነበር።
ሙሉውን አስነብበኝ ...ዳንኤል ግርማ This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.
አቶ ሠለሞን አየለ ”አንድነትም እንደ መአህድ - ብርቱካንም እንደ አሥራት” በሚል ርዕስ መአህድንና አንድነትን እያነፃፀሩ፤ በመአህድ የሆነው ሁሉ ዛሬ በአንድነት እየተፈፀመ መሆኑን ያሳዩበትን ጽሑፍ ኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ ላይ አነበብኩ። የኢትዮጵያ ፖለቲካ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ የማይመጣ ሁሌም በትናንት ዜማ የሚያቀነቅን፣ ፖለቲከኛ ነን ባዮችም ከትናንት ስለመማራቸው እያወሩ፤ በተግባር ግን ያንኑ የሚደግሙ በመሆናቸው አያሌ የለውጥ ጊዜያት እንደዘበት አምልጠውናል። የዛሬው ሁኔታቸውም ለነገ ተስፋ የሚሰጥ ሆኖ አይታይም። |