ሽማግሌና ሽምግልና (ፕ/ር መስፍን)

Prof. Mesfin W/Mariamፕሮፌሠር መስፍን ወልደማርያም (ጥር 2001 ዓ.ም.)

በብዙ ሚልዮን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ሽምግልና አድባር ነው፤ ከቤተሰብ ጀምሮ በትንሽም ማኅበረሰብ ውስጥ ግጭት አይጠፋም፤ የሚፈጠረውን ማናቸውም ዓይነት ግጭት ለማለሳለስና በስምምነት ለመተካት የሚደረገው ባህላዊ ሽምግልና በመልኩም በባህርዩም ዛሬ በሽምግልና ስም ከምናየው በጣም የተለየ ነው። በኢትዮጵያ ባህል ሽምግልና የሚነሳው ከመንፈሣዊ መሠረት ላይ ነው። ሽምግልና የአምላክ ተግባር ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቆሞ ከመሄድ በፊት ብዙ ጊዜ መውደቅ አለ (ዳኛቸው ቢያድግልኝ)

ዳኛቸው ቢያድግልኝ / ጥር 5 ቀን 2001 ዓ.ም.

ኢትዮጵያውያን እንኳን ደስ አላችሁ!

አንዳንዶቻችን አቤቱ ወደ ፈተና አታግባን እያልን ዳር በቆምንበት ሰዐት ፈተናችንን እንቀበል ዘንድ ብርታትን፣ በአሸናፊነት እንወጣው ዘንድ ጥበብን አብዝተህ ስጠን ያሉ ፈጥነው እየገሰገሱ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ካርል ማርክስና ምዕራባውያን (ፕ/ር መስፍን)

ፕሮፌሠር መስፍን ወልደማርያም (ታኅሳስ 2001 ዓ.ም.)

የካርል ማርክስ የፖለቲካ ፍልስፍና ሞተ ተብሎ፣ ወደ መቃብር ከገባ ሃያ ዓመት ሊሆነው ነው። ስለካርል ማርክስ በጻፍሁት ያልታተመ ጽሑፍ “በይሁዲነት ተወልዶ፣ በክርስቲያንነት አድጎ፣ በከሀዲነት የሞተ” በማለት የተገነባበትን ሁኔታ ለመግለጽ ሞክሬ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዎ! ለኢሮብ ህዝብ ኢትዮጵያዊነቱ የማይገሰስ ክብሩ ነው

የችግሩ ጥልቀት ካሳሰባቸው የኢሮብ ተወላጆች

እ.ኤ.አ. Dec. 22 ቀን 2008 “Tiny tribe Ethnic group claim Ethiopian allegiance in border row with Eritrea” በሚል ኤ.ኤፍ.ፒ. (AFP) ያወጣውን ዘገባ በአንክሮ ተመልክተነዋል። ኤ.ኤፍ.ፒ. የራሴ በሚለው መንግሥት ለተረሳው የኢሮብ ህዝብ ድምፅ ለመሆን በመብቃቱ ምስጋናችንን እናቀርባለን።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ብርቱካን የምትፈራው ፍርሀትን ብቻ ነው (ከአባኪያ)

ከጠላቶቿ የበለጠች፤ ያኮራችን ምስኪን ሴት

 

የነውር ጥግ፡ ሴት ደብዳቢ፤ አረጋዊ ረጋጭ

ይሄ የአንድነትም ብቻ አይደለም። ይሄ የኢህአዴጎችም ጭምር ነው። ይሄ የሴቶች ሁሉ ጉዳይ ነው። ይሄ ልጆች ያላቸው ሁሉ ጉዳይ ነው። ይሄ የእናቶች ሁሉ ጉዳይ ነው። ይሄ የክርስቲያኖች ብቻ አይደለም። ይሄ የእስላሞችም ብቻ አይደለም። ይሄ የኦሮሞዎች ብቻም አይደለም። ይሄ ኢትዮጵያዊያን ብቻም አይደለም። ይሄ የሂላሪ ክሊንተንም ነው። አልልላት ብሎ እንጂ ይሄ የአዜብ ጎላም ጭምር ነው።

የይቅርታ ዐዋጁ አተገባበር በወ/ት ብርቱካን ላይ (ያሸንፋል ፍቅሩ)

ያሸንፋል ፍቅሩ

የፍትህ ሚኒስቴር ታኅሳስ 20 ቀን 2001 ዓ.ም.፣ በስሙ ያወጣውና በመንግሥት መገናኛ ብዙኃን የተደመጠ፣ የተነበበው መግለጫ ለአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ለወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ፣ ሐምሌ 13 ቀን 2001 ዓ.ም በአገሪቱ ፕሬዝዳንት የተሰጣት ይቅርታ የተነሳው በራሱ በፍትህ ሚኒስቴር ውሳኔ መሆኑን የሚያመለክት ነው። መግለጫው ለይቅርታው መነሳት መሠረት ያደረጋቸውን የይቅርታ ሥነ-ሥርዓት ዐዋጅ ቁጥር 395/1996 16(253)ንም ጠቅሷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሙጋቤና የዚምባብዌ ህዝብ (ፕ/ር መስፍን)

Pfro. Mesfin W/Mariamፕ/ር መስፍን ወልደማርያም (ታኅሳስ 2001)

ፕሬዝዳንት ሙጋቤ የብዙዎቹ የአፍሪካ መሪዎች ዓይነተኛ አብነት ናቸው፤ ፕሬዝዳንት ሙጋቤ ሲጀምሩ የነፃነት ታጋይ አርበኛ ሆነው ነበር። በዚያን ጊዜ ሮዲዝያ በሚባለው ሀገር የሚኖሩ ነጮች፣ የደቡብ አፍሪካ ነጮችን አብነት ተከትለው፣ የነጮች የበላይነት የሠፈነበት አገዛዝ የዛሬ ሠላሳ ሦስት ዓመታት ግድም በጉልበት መሠረቱ፤ ሁለት የዚምባብዌ መሪዎች ጫካ ገቡና የትጥቅ ትግል ጀመሩ። የጎረቤት የአፍሪካ ሀገሮችና ሌሎችም እየረዱዋቸው፣ ውጊያቸውን ቀጠሉ፤ እንግሊዞች ባዘጋጁት እርቅ የትጥቅ ትግሉ አብቅቶ ወደ ሠላማዊ የፖለቲካ ትግል ገቡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እኛ ብንተባበር (ግርም ካሣ)

ይህን ሕግን የሚንቅ ሥርዓት ማስወገድ እንችላለን!

ግርም ካሣ (ቺካጎ) This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.  (ታህሳስ 24 ቀን 2001 ዓ.ም.)

ፕሮፌሠር መስፍን ወልደማሪያም ዋሽንግተን ዲሲ የአንድነት ፓርቲ ልዑክ ቡድን አባል ሆነው ለኢትዮጵያውያን ንግግራቸውን የጀመሩት በፀሎት ነበር። “አምላክችን ሆይ! ኢትዮጵያ ተቸግራለች። እኛም ተችግረናል። እባክህ ፍቅርን ስጠን!” ብለው እግዚአብሔርን ሲማጸኑ ከዓይኖቼ እንባ ፈሶ ነበር። በኢንተርኔት ብቻዬን እከታተል ስለነበረም ድምጼን ከፍ አድርጌ “አሜን!” ብዬ ጮህኩኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“የብሔርና የግለሰብ መብት ጥያቄ በኢትዮጵያ - ትናንትናና ዛሬ” በዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ

ባለፈው ሣምንት ቅዳሜ ታህሳስ 18 ቀን 2001 ዓ.ም. “መድረክ ለዲሞክራሲያዊ ምክክር በኢትዮጵያ” (የምክክር መድረክ) የተሰኘው ድርጅት በኢምፔሪያል ሆቴል ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ስድስት ምሁራን የውይይት ጽሑፍ ማቅረባቸውን መዘገባችን አይዘነጋም። የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት የነበሩት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳም አንዱ ጽሑፍ አቅራቢ የነበሩ ሲሆን፣ “የብሔርና የግለሰብ መብት ጥያቄ በኢትዮጵያ - ትናንትናና ዛሬ” በሚል ርዕስ የመወያያ ጽሑፋቸውን አቅርበዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“የፖለቲካ ድርጅቶች የሕብረት ጥያቄ በኢትዮጵያ - ትናንትና እና ዛሬ” ከስዬ አብርሃ

ባለፈው ቅዳሜ ታህሳስ 18 ቀን 2001 ዓ.ም. “መድረክ ለዲሞክራሲያዊ ምክክር በኢትዮጵያ” (የምክክር መድረክ) የተሰኘው ድርጅት በኢምፔሪያል ሆቴል ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ስድስት ምሁራን የውይይት ጽሑፍ ማቅረባቸውን መዘገባችን አይዘነጋም። አቶ ስዬ አብርሃ “የፖለቲካ ድርጅቶች የሕብረት ጥያቄ በኢትዮጵያ - ትናንትና እና ዛሬ” በሚል ርዕስ ጽሑፍ አቅርበዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...