በእውኑ ብርቱካን ከቴዎድሮስ ታንሳለችን?! (አባኪያ)

እውነት እውነት እላችኋለሁ - አታንስም!!

አባኪያ  

ብርቱካን፤ እነሆ ሌላ ታሪካዊ ቅጽበት መጣ። ታስሮ የሟሟ የለም። ቴዲም አልሟሟ። ዶ/ር ታዬም። ታምራትም እንዲሁ። አሁን ያ ታዬ እዚያው እንደታሰረ ቢቀር ይሻለው ነበር እዚህ ከሚርመጠመጥ። ሆነ ሀኦነነ፤ ብርቱካን ሆይ፤ ብትታሰሪ በቅሌት አይደለም። ወይም በስርቆት። ለመብትሽና ለኢትዮጵያዊያን መብት ባደረግሽው በምታደርጊው ተጋድሎ እንጂ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቫንኩቨር እየተሰናዳች ነው፤ ጀግናዋን ልታስብ፣ ለእስረኛዋ ልትመሰክር፣ የተገፉትንም ልትዘከር!

ቫንኩቨር እየተሰናዳች ነው፤ ጀግናዋን ልታስብ፣ ለእስረኛዋ ልትመሰክር፣ የተገፉትንም ልትዘከር

 

አሁን የምጣችን መሀል ላይ ነን። ይሄንን ለመረዳት ደግሞ “ጌታን መቀበል” የለብንም። ስለነጻነታችን፡ ሰዎች ይታሰራሉ። ስለ አንድነታችን ሰዎች ይገደላሉ። ስለ ፍትሀችንም ሰዎችም ይሰደዳሉ። አካላቸውም ተሰናክሎ ይቀራል። “እኛ ግን ምንም እንዳልተፈጠረ ሕይወታችንን እንቀጥላለን” ብለን ጽፈናል፤ ከዚህ በፊት። በርግጥ ክርስቶስ ስለሞተ፣ ነቢዩም ስላለፉ አለም መሽከርከሯን አላቆመችም። እኛ ቫንኩቨራዊያን ግን ይሄንን መለወጥ፣ ይሄንን መገልበጥ፣ ይሄንን መነቅነቅ ሻትን። ሰዎች በተገደሉ፣ ሰዎች በተሰደዱ፣ ሰዎች በታሰሩም ጊዜ ሕይወታችንን ብቻ ከማሳደድ አለማችንን ብቻ ከማሽከረከር ባሻገር፤ አለማችንን የምናቆምበት፤ በጭፈራችን ውስጥ፣ በልደታችን ውስጥ፣ በስብሰባችን ውስጥ፣ በደስታችንም ውስጥ ሁሉ፤ እነዚህን የተሰዉትን፣ የታሰሩትን፣ የተሰደዱትን፣ አካላቸውም የተሰናከለውን የምናስብበት ቅጽበት እንደሚያስፈልግ አምነን። እነሆ ቫንኩቨር እየተሰናዳች ነው። ሙሽሮቿን ልታስብ፣ ሙሽሮቿን ልትዘከር። ለታሰሩት አጋርነቷን ልትገልጽ። የኢትዮጵያን ግዛት ካካለለው ሰፊው እስር ቤት ወደ ጠባቡ ቃሊቲ ወይንም ዝዋይ ያለፍትህና በበቀል የተዘጋባቸውን ልታስብ እየተዘጋጀች ነው።

 አሁንስ የነኚህ ሰዎች ንቀት ጣሪያ ነካ። ቴዲ የመጀመሪያ አይደለም። ቴዲ የመጨረሻም አይደለም። ስንታሰር ኖረናል። ላልተወሰነ ጊዜም ስንታሰር እንኖራለን። ለዚህ ነው በምጣችን መሀል ላይ ነን ያልነው። እስራታችንን ለማሳነስ ከዚህ ከምእራቡ አለም የምንወረውረው ድንጋይ መለስ ዘንድ ባይደርስም እንኩዋን፤ የምንለግሰው ሞራል ግን ወዳጆቻችን ታጋዮቻችን ዘንድ ይደርሳልና፤ እዚያው ኢትዮጵያ ውስጥ የእስራታችንንም ቀንበር ለመስበር የሚታገሉትን ግን ከማሰብና ከማመስገን ከማበራታታም ወደኋላ አንልም። ታጋዮች ሲረሱ ያማቸዋል። ይጸጸታሉ። ቴዲ በዘፈኑ እንዲጸጸት አንፈልግም። ምነው ባልዘፈንኩ እንዲል አይሻም፡ ማህበረ-ቫንኩቨራዊያን። እንኩዋን ዘፈንኩ፤ እነሆ ትውልድ ሁሉ ያስታውሰኛል እንዲል እንጂ።

የቴዲ መታሰር ልክ እንደ ኦባማ መመረጥ “Symbolic” ነው። የኦባማ መመረጥ ግን ለብዙዎች የባርነት ቀንበር የመሰበሩን፣ የቀለም መጋረጃ መቀደዱን፣ የእኩልነት ዳር መጀመሩን፣ የዘር መድለዎ ማብቂያ መቃረቡን፣ ያ ማርቲን ሉተር ኪንግ ያለመው የተራራ ጫፍ መድረሳቸውን ምሳሌ ያበስራል። የቴዲ አፍሮ መታሰርም፤ በተቃራኒው ቢሆንም ምሳሌያዊ ነው። ይሄ የተበላሸ ስርአት የሰዎችን ሀሳብ ለማፈን የት ድረስ እንደሚወርድ የሚያሳይ ነው። የነዚህን ሰዎች ቂመኝነትና በመንግስታችን ከመጣ ዘፋኝም ይሁን ቄስ፤ ለማኝም ይሁን መምህር፤ ህጻንም ይሁን አዋቂ አንተውም አመለካከት ያሳያል። ጠብ-መንጅ አነስተው ተኮሱብን፣ ቦንብ አፈነዱብን፣ ዘር አጠፉ ወይም ለማጥፋት ሞከሩ አንድ ነገር ነው። ሰው ዘፈነ ተብሎ እንዴት ይታሰራል። እንዴት ያለ የዴሞክራሲ ጥግ ላይ ደረስን ጎበዝ? “ደጉ ይገልጣልን ድጋሜ ገደሉት” አለ በቴዲ አፍሮ መታሰር ያዘነው አበበ በለው። ስለዚህም ነው የቴዲ መታሰር የዚህ ስርአት ወጥ መርገጥ ሌላ ምሳሌ ነው ያልነው። የታሰሩትን ማሰብ ደግሞ በሰማይም በምድርም መልካም ነው። ሰምታችሁ ጠግባችሁት ይሆናልና። ያንን የመጽሀፍ ጥቅስ አላነሳላችሁም። “ስታሰር አልጠየቃችሁኝም፣ ስታመም አልጎበኛችሁኝም፣ ስራብ አላበላችሁኝም …” ይመጣል።

 

ቴዲ አይሟሟም። ባይታሰር መልካም ነበር። ቢታሰርም ግን ቀድሞውን እስር ቤት ነው። የቴዲ ጀግንነቱም ኢትዮጵያዊነትንና ፍትህን የሚሰብኩ ዘፈኖችን መዝፈኑ ብቻ አይደለም። እነዚህን ሰዎች የሚናደፍ ዘፈን ዘፍኖ እዚያው እኛ በሰበብ አስባቡ ጥለናት ከሸሸነው ኢትዮጵያ ሙጭጭ ማለቱ ነው። ሰው ገደልክ ብለው ቢከሱትም እንኩዋን፤ እዚህ እምእራብ፣ ከእኛ ምኩራብ ሊቀር አልፈለገም። “ቀድሞውንም ከሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ጋር ታስሯል” አለ አንዱ ወዳጃችን። ልዩነቱ የአሁኑ እስር ቤት ጠበበ። ቴዲና ሀሳቡ፣ ቴዲና የዘመረለት ፍቅር፤ የዘመረለት የእኩልነትና የፍቅር ራእይ ግን አይታሰሩም። ያሳወቀኝ ያ ህዝብ ነው። ያከበረኝም ያ ምስኪን የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው። ከኢትዮጵያ ብርቅ ቀኟ ይራቀኝ ብሎ እዚያው አገሩ ከተመ። እስሩን አጠበቁበት። የሱንም የሌሎችንም ሞራል ለመንካት። የገረመንስ የዚህ ልዑል የሚባል የገብረማሪያም ሳይሆን የገብረ ሰይጣን ልጅ ነው። ልጆች የሉትም? ሚስት የለችውም? እቁብና እድር፤ ማሀበር የለውም? ጽዋም አይጠጣም? ነው ወይስ እቁቡን ወደነአላሙዲ አዞረ? መቼም እዚህ ቁጭ ብለን እንደው በደፉት አንልም። ግን ይሄ “ዳኛ” ሳይሆን መጋኛ ነው። ሽብርተኛ። ሕወሀት-ሰራሽ ሽብርተኛ። ሽብርተኛ ደግሞ በተገኘበት ዋጋ ይሰጠዋል። ይሄን መጋኛ በጸበልም ይሁን በመስቀል ለሚያጋጭልን ኢትዮጵያ ዛሬም ባይሆን አንድ ቀን ሽልማት ትሰጣለች።

  

ይህ የእስራት ጥግ ነው። እስከዚያው ግን ቴዲንም ይሁን ሌሎች ንጹሀንን ያሰሩ፣ የገደሉ፣ ያሰቃዩ፣ ወይንም በዚህ የመግደልና የማሰቃየት ሂደት የተባበሩ በሙሉ ለፍርድ እስኪበቁ፤ እነሆ የሁለት ሺህ አስር የኦሊምፒክ አዘጋጅ፤ ታላቋ ቫንኩቨር እየተሰናዳች ነው። ቅዳሜ December 27th 2008 ቴዲንና መሰል የህሊና እስረኞችን ለማሰብ፤ ለህሊና እስረኛዋ፣ ለሙሽራዋ አጋርነትዋን ልትገልጽ ላይ ታች እያለች ነው። ሁላችሁም ተጋብዛችኃል። ያደረሳችሁ ሁሉ ኑ። ኑ እና በቴዲና መሰል ዘፈኖች እንጫወት። እንድትመጡም ብቻ አይደለም አሁን ባያደርሳችሁም በያላችሁበት ሰልፋችሁን፣ ዝክራችሁን፣ እንደቴዲ ዘፈን “ኡኡታችን” እስኪሰማ ኡኡታችንን እንድንቀጥልም ጭምር እንጂ። በድግሳችሁ ሁሉ ቴዎድሮስን አሰቡት። ይሄ ምክንያትም ነው። እንደ ኦባንግ፤ እንደ ኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ ያሉ ድርጅቶችን ለመርዳት መልከም አጋጣሚም ነው። ያም ብቻ አይደለም። ሕዝባዊ ወያነ አርነት ትግራይ እንዲህ ያለውን ስራ እስከገፉበት፤ እኛም አንተኛም፤ ብንተኛም አናንቀላፋም፣ ብንጨፍርም ቴዲንና መሰል የህሊና እሰረኞችን አንረሳቸውም ለማለትም ጭምር ነው። ቫንኩቨራዊያን። በቴዲም ይሁን በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እስራቱ በጠበቀ ቁጥር እኛም ቴዲንና መሰል እስረኞችን የጀግና ማእረግ እንሰጣቸዋለን። የአርበኝነት። የትግላችን ፊታውራሪነት። ቫንኩቨራዊያን።

 

አንድ ዕይታ አስራ አንድ አስተያየቶች፤ ስለቀጣይ “ምርጫ” እና ቀጣይ የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች አካሄድ

“ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መሳተፍ፤ መግባት አለባቸው” ተክለሚካኤል አበበ

በ2010ም እ.ኤ.አ. ይሁን ከዚህ በኋላ፡ መቼም “ምርጫ” ከተካሄደ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በኢህአዴግ መንግሥትነት በሚካሄድ ማናቸውም ምርጫ መሳተፍ ይገባቸዋልን? የሚለውን ጥያቄ፡ “አዎ መሳተፍ አለባቸው!” ብቻ ሳይሆን “ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መሳተፍ፤ መግባት አለባቸው” ማለቴ ብዙዎቻችሁን ሳያስገርም ምናልባትም ይሄ ሰው ምን ነካው? ጤነኛም አይደል እንዴ ሳያሰኛችሁ አይቀርም። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሕገ መንግሥትና ሕገ አራዊት (ፕ/ር መስፍን)

ፕሮፌሠር መስፍን ወልደማርያም (ታኅሳስ 2001)

Prof. Mesfin Woldemariam“ሕገ አራዊት” የተፈጥሮ ሕግ ነው፤ በደመ-ነፍስ የሚንቀሳቀሱ ኹሉ ለመራባት የሚያስችላቸውን ግዴታቸውን የሚፈጽሙት በሕገ አራዊት ነው። የቀደመው አሁን ከአለው አይለይም፤ የወደፊቱ ከአሁኑ እንደማይሻል የታወቀ ነው። የቀድሞውም በጉልበት ነው፤ የአሁኑም በጉልበት ነው፤ የወደፊቱም በጉልበት ነው። የሕገ አራዊት መሠረቱ ጉልበት ብቻ ነው። ምግብ የሚገኘው በጉልበት ነው፤ ጉልበት ያለው ይበላል፤ ጉልበት የሌለው ለጉልበተኛው ምግብ ይሆናል፤ ጉልበት ያለው ይንደላቀቃል፤ ጉልበት የሌለው በየጉድጓዱ ይሽሎከለካል። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሽምግልና ወይስ የሕግ የበላይነት? (ነብዩ ግዛው)

ነብዩ ግዛው

በእንቢልታ ጋዜጣ ቅጽ 1 ቁጥር 49 እትም ”የፖለቲካ ውዝግቡና የሽማግሌዎች ሚና” በሚል ርዕስ የቀረበውን ዘገባ አንብቤዋለሁ። ጹሑፉ በጣም ጥሩና ሊነበብ የሚገባው ሲሆን፣ በውስጡ ቢካተት የበለጠ ጥሩ ይኾን ነበር ያልኩትን፤ ይችን ጽሑፌን ለአንባቢ እንድታደርሱልኝ እጠይቃለሁ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የምርጫ ሌባ (ፕ/ር ዓለማየሁ ገ/ማርያም)

ሌባ! ሌባ! ያዘው የምርጫ ሌባ!

Prof. Alemayehu G.Mariamፕሮፌሠር ዓለማየሁ ገ/ማርያም

የታይላንድ ሕገ መንግሥታዊ ፍ/ቤት ባለፈው ሣምንት በምርጫ ያጭበረበሩ ሌቦችን ጉዳይ ተመልክቷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ሶምቻይ ዎንግስዋትና የስድስት ጥምር ፓርቲው አመራሮች በታኅሳስ 2007 ዓ.ም. በሀገሪቱ የተካሄደውን ምርጫ አጭበርብራችኋል በሚል ጥፋተኛ ብሏቸዋል። ግለሰቦቹ ጥፋተኛ የተባሉት የመራጮችን ድምፅ በመግዛት፣ ድምፅ በማጭበርበር፣ መራጮች የሚሰጡትን ድምፅ በማሳሳትና ሌሎች የምርጫ የማጭበርበር ተግባራት በመፈፀም ነው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ክፋትን የዘሩ መከራን ያጭዳሉ (ዳኛቸው ቢያድግልኝ)

ዳኛቸው ቢያድግልኝ (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. )

የፖለቲካ አመለካከትና አስተሳሰብ ሳይሆን ዛሬ ኢትዮጵያዊነት ወንጀል ነው። ፍቅር አያስከብርምና ይኸው ዛሬን ደግሞ ፍቅርን፣ መተሳሰብን፣ ይቅር መባባልን አሳስረን የእስር ቤታችንን አጥር እያጠባበቅን ነው። የፈራን ፈርተን ዳግም ቀና እንዳንል ስንረገጥ ታፋችንን በፈረቃ ለመስጠት ፈቃዳቸውን እየጠበቅን ’የባሰ አታምጣ!’ እንላለን። የመረጥነውን እምቢ ሲሉን ዝም ባልን፣ የመረጥናቸውም ግራ ሲጋቡብን ወደ ’አንድ ሁኑ!’ ማለት ባይቻለን ዛሬ ከቀሳውስቱ ልቆ ምህረትን የለመነ፣ ከጠቢባን ልቆ ፍቅርን የሰበከና በሚፈነጭበት ዕድሜው ብስለትን ያስመለከተ ወንድማችንን ለስድስት ዓመት ሊነጥቁን መወሰናቸውን ነገሩን። እግረ መንገዳቸውንም ’እስቲ የምትሆኑትን እናያለን’ ብለው እንደ ጠገበ ጅብ እያስካኩብን ነው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የቴዲ ጥፋቱ ያስተሰርያል ማለቱ! (ኤፍሬም ማዴቦ)

ኤፍሬም ማዴቦ (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. )

በ1999 ዓ.ም. በተደረገው ህዝባዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ህዝብ ይበጁኛል ብሎ የመረጣቸውን የህዝብ ተወካዮች በግፍ አስሮ ለሁለት ዓመታት ካሰቃየ በኋላ በይቅርታ ተለቃችኋል ብሎ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ያሾፈው የመለስ ዜናዊ መንግሥት ከሰሞኑ ውዱን የኢትዮጵያ ልጅ ቴዎድሮስ ካሳሁንን (ቴዲ አፍሮን) ካለ በቂ ምክንያት አስሮ፣ ካለ በቂ ማስረጃ ጥፋተኛ ነህ ብሎ ፈርዶበታል። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የቴዲ ክስ - እኛ ሁላችንም ነው የተፈረደብን

ግርማ ካሣ (ከቺካጎ)

ሚያዚያ 8 ቀን 2000 ዓ.ም. ነበር ዝነኛው የኪነት ሰው ቴዎድሮስ ካሳሁን “ሰው ገጭተሃል” በሚል ክስ ነው ወህኒ የወረደው። እስር ቤት በገባ በስምንት ቀኑ “በርግጥ መንግሥት መረጃ ኖሮት ነውን? ወይስ ቴዲ የገዢው ፓርቲ ሰዎች ህዝብ እንዲሰማ የማይፈልጉትን መልዕክቶች በማቅረቡ? በርግጥ ሕግ የበላይ መሆን ስላለበት ነውን? ወይስ ሕግን እንደ ዱላ ተጠቅሞ የተቀየሙትንና የማይስማማቸውን ሰው ለማፈንና ለማስወገድ ስለተፈለገ ነውን? በኢትዮጵያ ፍትህ እንዲሰፍን፣ ሁሉም በሕግ ፊት እኩል ስለሆኑ ነውን? ወይስ በኢትዮጵያነት ላይ ያነጣጠረ ጥቃት?” የሚሉ ጥያቄዎችን በመጠየቅ መልሱን በቅርብ የምናየው እንደሆነ ገልጨ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሽምግልናውና ሽማግሌዎቹ

 የቅንጅት አመራሮችን ከእስር በማስፈታት ኺደት የተሳተፈው የሽምግልና ቡድን፣ የኃይማኖት አባቶችንም እርስ በርሳቸውና ኦነግን ከመንግሥት ጋር ለማደራደር፤ ከኦነግ ጋር በተያያዘ በቁጥር ስር የዋሉ እስረኞችን ለማስፈታት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። በሌላ በኩል ኦነግን ከመንግሥት ጋር ለማደራደር ሦስት አባላት ያሉት ሌላ ቡድንም ተቋቁሟል። እነዚህ የሽምግልና ቡድኖች በሀገራዊው ተጽዕኖ ላይ ምን ዓይነት የፖለቲካ ድባብ ያሳድራሉ? ስትል የሚመለከታቸውን የተለያዩ ሰዎች የጠየቀቸው የእንቢልታ ጋዜጣ ዘጋቢ ጽዮን ግርማ ስትሆን፤ ጋዜጣው ይህንኑ ዘገባ ለንባብ አብቅቷል። ሙሉውን አስነብበኝ ...