በእውኑ ብርቱካን ከቴዎድሮስ ታንሳለችን?! (አባኪያ)
እውነት እውነት እላችኋለሁ - አታንስም!!
አባኪያ
ብርቱካን፤ እነሆ ሌላ ታሪካዊ ቅጽበት መጣ። ታስሮ የሟሟ የለም። ቴዲም አልሟሟ። ዶ/ር ታዬም። ታምራትም እንዲሁ። አሁን ያ ታዬ እዚያው እንደታሰረ ቢቀር ይሻለው ነበር እዚህ ከሚርመጠመጥ። ሆነ ሀኦነነ፤ ብርቱካን ሆይ፤ ብትታሰሪ በቅሌት አይደለም። ወይም በስርቆት። ለመብትሽና ለኢትዮጵያዊያን መብት ባደረግሽው በምታደርጊው ተጋድሎ እንጂ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
“ሕገ አራዊት” የተፈጥሮ ሕግ ነው፤ በደመ-ነፍስ የሚንቀሳቀሱ ኹሉ ለመራባት የሚያስችላቸውን ግዴታቸውን የሚፈጽሙት በሕገ አራዊት ነው። የቀደመው አሁን ከአለው አይለይም፤ የወደፊቱ ከአሁኑ እንደማይሻል የታወቀ ነው። የቀድሞውም በጉልበት ነው፤ የአሁኑም በጉልበት ነው፤ የወደፊቱም በጉልበት ነው። የሕገ አራዊት መሠረቱ ጉልበት ብቻ ነው። ምግብ የሚገኘው በጉልበት ነው፤ ጉልበት ያለው ይበላል፤ ጉልበት የሌለው ለጉልበተኛው ምግብ ይሆናል፤ ጉልበት ያለው ይንደላቀቃል፤ ጉልበት የሌለው በየጉድጓዱ ይሽሎከለካል።
ፕሮፌሠር ዓለማየሁ ገ/ማርያም 


