የፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳን መጽሐፍ ለምትተቹና ለምትቃወሙ
”የኦሮሞ እና የአማራ እውነተኛው የዘር ምንጭ” የተሰኘውን የፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳን መጽሐፍ የምትተቹና የምትቃወሙ፤ ኢትዮጵያን ባለማወቅ፣ ከቅናትና ምቀኝነት በተነሳ ሃሰት ነው
ይሁነው አሰፋ
አስተያየትና መተቸት አግባብ ያለው ተመክሮ ሆኖ ሳለ በተለይ ሦስት ሰዎች የተቻችሁትና ያቀረባችሁ ነቀፌታ ከእውነትና ሃቅ እጅግ የራቀ ከመሆን ጋር፤ ከቅናትና ምቀኝነት የተነሳ ውሸትና ሃሰትን ያካተተ ለመሆኑ በጉልህ አሳይቶባችኋል። እውነትን ፈላጊ ትክክለኛ ነገሮችን የሚሻ፣ እንዲሁም የተማርንና አወቅን ከሚሉ፣ እኩል የትምህርት ችሎታና ማዕረግ፣ ኢትዮጵያንና ታሪኳንም እናውቃለን ከምትሉ፤ በተለይ ከፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌና ፕሮፌሰር ጳውሎስ ሚልክያስ በመጽሐፉ ላይ የሰነዘራችሁት አስተያየት እጅግ በጣም ዝቅ ያለ ትምህርታዊ ተመክሮን፣ ክብርና ማዕረግን ያልተከተለ ሥነ-ምግባርና ፕሮፌሽናሊዝምን ያጓደለ ነው። ከዚህም የተነሳ የሰነዘራችሁት ትችት፣ አስተያየትና ተቃውሞ ትምህርታዊ እርማትን የሚያመጣ ሳይሆን፤ አሉባልታና ተራ ነቀፌታ፣ ቅናትና ተንኰልን የሚያንጸባርቅ በመሆኑ በብዙ ታዛቢዎች ዘንድ ቅሬታንና ኀዘንን አሳድሮብናል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...