ጠ/ሚ መለስ ሚኒስትሮቻቸውን አጸደቁ

አቶ ስዩም መስፍን በአቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ተተክተዋል

Ethiopia Zare (ማክሰኞ መስከረም 25 ቀን 2003 ዓ.ም. October 5, 2010)፦ በ2002 ዓ.ም. በተካሄደው ምርጫ መሰረት በብቸኛው ፓርቲ ኢህአዴግ ለመጭው አምስት ዓመታት የምትመራው ኢትዮጵያ ከትላንት ሰኞ ጀምሮ በተካሄደ የፓርላማ ተመራጮች ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ አፈ ጉባዔ፣ ም/ጠቅላይ ሚኒስትርና ሌሎች የካቢኔ አባላትን አጸደቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የስታር አሊያንስ አባል ሆነ

Mr. Jaan AlbrechtAto Girma WakeEthiopia Zare (ሐሙስ መስከረም 20 ቀን 2003 ዓ.ም. September 30, 2010)፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ”ስታር አሊያንስ” የተሰኘውን ዓለም አቀፍ የአየር መንገዶች ሕብረት በሚቀጥሉት 12 ወራት ለመቀላቀል ረቡዕ መስከረም 19 ቀን 2003 ዓ.ም. ተፈራረመ። አየር መንገዱ ከግብፅ እና ከደቡብ አፍሪካ ቀጥሎ ሕብረቱን ሲቀላቀል ሦስተኛው የአፍሪካ አየር መንገድ ይሆናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የጸደንያ ማሪያም ንግስ በቫንኩቨር ደምቆ ተከበረ

የጸደንያ ማሪያም ንግስ በቫንኩቨር ከሲያትል፣ ፖርትላንድ ካልጋሪና አሪዞና ምእመናን ተሰባስበው ነበር

በየአመቱ የሚከበረው የጸደንያ ማሪያም ንግስ አቡነ ሉቃስ፣ አቡነ ዩሀንስ፣ አቡነ ሚካኤል (ከካልጋሪ)፣ ሁለቱ አባ ገ/ስላሴዎችና የቫንኩቨር ቅድስት ድንግል ማሪያም ደብር አባት መልአከ ጸሃይ አፍወርቅና አምስት መቶ የሚጠጉ ምእመናን በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ መከበሩ ተገለጸ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ በስዊድን ቆይታ አደረጉ

Dr. Negasso Gidada ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳየሶሻል ዲሞክራት ፓርቲ ኃላፊዎችንና ኢትዮጵያውያንን አነጋገሩ

Ethiopia Zare (ቅዳሜ መስከረም 8 ቀን 2003 ዓ.ም. September 18, 2010)፦ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት፣ የአሁኑ የመድረክ የውጪ ኮሚቴ አባል፣ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበርና የውጪ ጉዳይ ኮሚቴ ሰብሳቢ የስዊድን ሾሻል ዲሞክራት ፓርቲ ባደረገላቸው ጥሪ መሰረት ካለፈው ረቡዕ ጳጉሜን 3 ቀን ጀምረው በስቶክሆልም በመገኘት እንቁጣጣሽን ከኢትዮጵያውያን ጋር አብረው አሳለፉ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

በስቶክሆልም በአይነቱ ልዩ መንፈሣዊ ጉባዔ ተካሄደ

ፍቅረሥላሴ አቢይ (ከስቶክሆልም)

በሰሜን አውሮፓ ሀገረ ስብከት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ፤ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ተዘጋጅቶ የነበረው የሦስት ቀን ጉባዔ በታላቅ ድምቀት ተጠናቀቀ። … (ሙሉውን ጽሑፍ በፒ.ዲ.ኤፍ. ለማንበብ እዚህ ይጫኑ!)

የኢትዮጵያ ታሪካዊ ቅርሶች በአደጋ ውስጥ ናቸው ተባለ

Ato Belachew Chekeneታምሩ ገዳ (ከለንደን)

ኢትዮጵያን በዓለም በታሪክ እና በቅርስ ባለቤትነት ተጠቃሽ ከሆኑት ጥቂት ሀገሮች መካከል አንዷ እንድትሆን ያደረጓት ታሪካዊ እና ኃይማኖታዊ ቅርሶቿ እጅግ አስጊ በሆነ የመጥፋት አዝማሚያ ውስጥ መሆናቸው ተገለጸ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቫንኩቨር በመጀመሪያው የኢትዮጵያዊያን የበጋ ፌስቲቫል ደምቃ ዋለች

በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ካናዳዊያንና አሜሪካዊያን ተገኝተው ነበር

“ብርቱካን መፈታት አለባት” የካናዳ ፓርላማ ተመራጭ ሚስተር ፒተር ጁሊያን

በቫንኩቨር ካናዳ ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው የኢትዮጵያ የክረምት ፌስቲቫል ከአሁን ቀደም ታይቶ በማይታወቅ መልኩ በፖለቲካ በሀይማኖትና በተለያዩ የማህበራዊ ችግሮች ምክንያት ተራርቆ የነበረው ነዋሪ በሙሉ በአንድ ላይ በመሰባሰብ በደማቅ ሁኔታ መከበሩ ታወቀ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ”ኢሳት” ቶምቦላ ወጣ፤ አሜሪካኖች ከፍተኛውን እጣ ወስደዋል

ካናዳዎችና አውሮፓዎችም ከእጣው ተጋርተዋል

ከጁላይ 29 እስከ ጁላይ 31 በአምስተርዳም በተካሄደው 8ኛው የኢትዮጵያዊያን አውሮፓውያን ስፖርትና ባህል ፌስቲቫል ላይ እንዲወጣ ታስቦ ለኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን (በምህጻረ ቃሉኢሳት”) መርጃ የተዘጋጀ ቶምቦላ ቅዳሜ ጁላይ 31 ቀን ከምሽቱ 8 ሰዓት አካባቢ አያሌ የኢሳት ደጋፊዎችና ጥቂት ተቃዋሚዎች በተገኙበት ወጣ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሌ/ኰ መንግሥቱ ኃይለማሪያም መጽሐፍ በኦፊሴል ነገ ገበያ ላይ ይውላል

L.Colonel Mengistu H.Mariamበዛሬው ዕለት ገበያ ላይ የዋለው ሁለት ሺህ ቅጂ በአንድ ሰዓት ውስጥ አለቀ

Ethiopia Zare (ዓርብ ሐምሌ 16 ቀን 2002 ዓ.ም. July 23, 2010)፦ በጋዜጠኛና ፀሐፊ ገነት አየለ የተዘጋጀው ”የሌተና ኰሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ትዝታዎች (ቁጥር 2)” መጽሐፍ ነገ ቅዳሜ ሐምሌ 17 ቀን 2002 ዓ.ም. (ጁላይ 24 ቀን 2010 እ.ኤ.አ.) በኦፊሴል ገበያ ላይ ይውላል። ዛሬ ማምሻውን በጥቂቱ ለሽያጭ የቀረበው ሁለት ሺህ ቅጂ በአንድ ሰዓት ውስጥ ተሸጦ ማለቁን ከአዲስ አበባ የኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ ሪፖርተር ዘግቧል። ሙሉውን አስነብበኝ ...

በዩጋንዳ-ካምፓላ ሁለት ፈንጂዎች ፈንድተው ከ64 በላይ ሰዎች ሞቱ

አንዱ ፈንጂ በኢትዮጵያዊያን ሬስቶራንት ውስጥ ፈንድቷል

Ethiopia Zare (እሁድ ሐምሌ 4 ቀን 2002 ዓ.ም. July 11, 2010)፦ በዩጋናዳዋ መናገሻ ካምፓላ ራግቢ ክለብ በተባለ ቦታና የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ውድድርን ለመከታተል በአንድ የኢትዮጵያ ሬስቶራንት ውስጥ በተሰባሰቡ ሰዎች መሀል በፈነዱ ሁለት ፈንጂዎች ምክንያት በርካታ ኢትዮጵያኖችን ጨምሮ 64 ሰዎች መሞታቸው ተገለጸ። ሙሉውን አስነብበኝ ...