በኃይሌ ገብረሥላሴ ጡረታ መውጣት አስተያየቶች እየጎረፉ ነው

የኒው ዮርኩን ማራቶን አትሌት ገብሬ ገብረማሪያም አሸነፈ
Ethiopia Zare (ሰኞ ጥቅምት 29 ቀን 2003 ዓ.ም. November 8, 2010)፦ አንጋፋው አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ ትላንትና በተካሄደው የኒው ዮርክ ማራቶን ውድድር ላይ በተሰማው ሕመም ምክንያት አቋርጦ ከወጣ በኋላ በሰጠው መግለጫ ራሱን ከአትሌቲክስ ጎራ ጡረታ እንደሚያወጣ ይፋ አደረገ። በአስደንጋጩ የአትሌት ኃይሌ ውሳኔ የተለያዩ አስተያየቶች እየጎረፉ መሆኑን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...

ማትያስ ከተማ
”አልተሳሳትኩም፣ ሐውልት ማሠራት በእኔ አልተጀመረም” አቡነ ጳውሎስ
የአዲስ አድማስ ጋዜጣ አዘጋጅ የሆነችው ጋዜጠኛ ጽዮን ግርማ የወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ከእስር በተፈታችበት ዕለት ከቃሊቲ እስር ቤት ጀምሮ ፈረንሣይ በሚገኘው መኖሪያ ቤትዋ ድረስ የነበረውን ትዕይነት በዚህ ሪፖርቷ ታስቃኘናለች። የአንድነት አመራሮች (እነ ኢ/ር ግዛቸው) እንዲሁም የመርኅ ይከበር አባላት (እነ ፕ/ር መስፍን) በወ/ት ብርቱካን ቤት መገናኘትን፣ የፖለቲከኞቹን አስተያየት፣ የህዝቡንና የአካባቢውን ሰዎች አስተያየት ታስነብበናለች። ወ/ት ብርቱካን ለጠ/ሚ መለስ ዜናዊ የፃፈችውን ደብዳቤ፣ የመንግሥት መገናኛ ብዙኀኑን ዘገባ፣ በተለይም በሰነዱ አንደምታ ላይ እና በ”ይቅርታው” ጉዳይ ላይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፍልስፍና እና የኢንስቲትዩት ኦፍ ሂዩማን ራይት መምህር የሆኑት ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋን አናግራለች። ዶ/ር ዳኛቸው ሰነዱን ከአራት ነጥቦች አንጻር በመመዘን ሰፋ ያለ ትንታኔ ሰጥተዋል። ይህንን ሰፋ ያለ ሪፖርታዥ ታነቡ ዘንድ እንጋብዛለን! … መልካም ንባብ! 



