በኃይሌ ገብረሥላሴ ጡረታ መውጣት አስተያየቶች እየጎረፉ ነው

Haile Gebrselassie of Ethiopia crossed the finish line at the Berlin Marathon on Sunday Sep. 28, 2008, setting a new world record.

የኒው ዮርኩን ማራቶን አትሌት ገብሬ ገብረማሪያም አሸነፈ

Ethiopia Zare (ሰኞ ጥቅምት 29 ቀን 2003 ዓ.ም. November 8, 2010)፦ አንጋፋው አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ ትላንትና በተካሄደው የኒው ዮርክ ማራቶን ውድድር ላይ በተሰማው ሕመም ምክንያት አቋርጦ ከወጣ በኋላ በሰጠው መግለጫ ራሱን ከአትሌቲክስ ጎራ ጡረታ እንደሚያወጣ ይፋ አደረገ። በአስደንጋጩ የአትሌት ኃይሌ ውሳኔ የተለያዩ አስተያየቶች እየጎረፉ መሆኑን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ

 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

”ሂሩት በቀለ ሞተች” የሚባለው ወሬ ሐሰት መሆኑ ተረጋገጠ

Hirut Bekele ሂሩት በቀለ ለአዲስ ድምፅ ራዲዮ ቃለምልልስ ሰጠች

Ethiopia Zare (ሐሙስ ጥቅምት 25 ቀን 2003 ዓ.ም. November 4, 2010) ፦ ”ታዋቂና ተወዳጅዋ አርቲስት ሂሩት በቀለ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች” ሲል በአሜሪካን ሀገር የሚገኘው ”የሀገር ፍቅር ራዲዮ” ባለፈው ቅዳሜ ጥቅምት 20 ቀን 2003 ዓ.ም. ያሠራጨውን ዘገባ ተከትሎ ወሬው ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ተዳርሶ ከፍተኛ ኀዘን በኢትዮጵያውን ዘንድ ተፈጥሮ ነበር። ዜናው ሐሰት መሆኑንና አርቲስቷ በሕይወት እንደምትገኝ ከአዲስ ድምፅ ራዲዮ ጋር ቃለምልልስ በማድረጓ ተረጋግጧል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአክብሮትና የሰማዕታት መታሰቢያ ቀናት እንደሚከበሩ ተገለጸ

Judge Woldemichael Meshesha, ዳኛ ወልደሚካኤል መሸሻ ማትያስ ከተማ

Ethiopia Zare (ረቡዕ ጥቅምት 24 ቀን 2003 ዓ.ም. November 3, 2010)፦ የፊታችን ቅዳሜ ጥቅምት 27 ቀን 2003 ዓ.ም. (ኖቬምበር 6 ቀን 2010 እ.ኤ.አ.) በስዊድን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳን መፈታት አስመልክቶ ”የአክብሮት ቀን” ብለው የሚያከብሩ ሲሆን፣ እሁድ ጥቅምት 28ን (ኖቬምበር 7ን) ደግሞ ምርጫ 97ን ተከትሎ ለተጨፈጨፉት የሰማዕታት ቀን መታሰቢያ ሊያከብሩ ነው። በዝግጅቱ ላይ ዳኛ ወልደሚካኤል መሸሻ ይገኛሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሲኖዶሱ የአቡነ ጳውሎስ ሐውልት እንዲፈርስ ወሰነ

በአንድ ራስ ሁለት ምላስ - አቡነ ጳውሎስ

Abune Paulos, አቡነ ጳውሎስ”አልተሳሳትኩም፣ ሐውልት ማሠራት በእኔ አልተጀመረም” አቡነ ጳውሎስ

”ሐውልት መሠራቱን አላውቅም፤ ሐውልቱ ሲገለጥ ነው ያየሁት” አቡነ ጳውሎስ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ጥቅምት 16 ቀን 2003 ዓ.ም. October 26, 2010)፦ አዲስ አበባ ጉባዔ ላይ የተቀመጠው ቅዱስ ሲኖዶስ ከብዙ የአባቶች ውትወታ በኋላ ስለ ሐውልታቸው ጉዳይ ዛሬ ምላሽ የሰጡት አባ ጳውሎስ፤ ሁለት የተጻረሩ ሃሳቦችን በማቅረብ መደናገር እንዲፈጠር ቢያደርጉም፤ ሲኖዶሱ ሐውልታቸው እንዲፈርስና ፖስተሮቹም ከተሰቀሉበት እንዲነሱ ወሰነ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያው ሲኖዶስ ጠቅላላ ጉባዔ ውጥረት ላይ ነው

አቡነ ጳውሎስ ስለሐውልታቸውና ፖስተሮች ጉዳይ ነገ ምላሽ እሰጣለሁ አሉ

Ethiopia Zare (ሰኞ ጥቅምት 15 ቀን 2003 ዓ.ም. October 25, 2010)፦ ባለፈው ሣምንት ዓርብ በአዲስ አበባ የተጀመረውና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሲኖዶስ ጠቅላላ ጉባዔ በተለያዩ የቤተ ክርስቲያኗ ችግሮች ላይ ውይይት ያደረገ ሲሆን፣ በተለይ በአቡነ ሳሙኤልና በአቡነ ጳውሎስ ሐውልት ማሰራት ጉዳይ ላይ ሰፊ ክርክሮች እየተደረጉ መሆኑ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ እንድትፈታ ለተሟገቱ ካናዳዊያን የምስጋና ዝግጅት ተሰናዳ

በተለይ ክቡር ሚስተር ፒተር ጁሊያንና ፓርቲያቸው አብዩን ሚና ተጫውተዋል

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ጥቅምት 6 ቀን 2003 ዓ.ም. October 16, 2010)፦ ብርቱካን ሚደቅሳ ከእስር እንድትፈታ የካናዳን ፓርላማ በመወትወት የሚታወቁትና የበርናቢ ኒውዌስት ሚኒስትር የኤን. ዲ. ፒ. ፓርቲ የፓርላማ ተመራጭ የሆኑት ክቡር ሚስተር ፒተር ጁሊያንንና አጋሮቻቸውን የሚያከብርና ለብርቱካን መፈታት ያደረጉትን አስተዋጽኦ የሚያደንቅ የምስጋና ስነስርአት በቫንኩቨር ነዋሪዎች መዘጋጀቱ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

”ወ/ሪት ብርቱካን ፖለቲከኛ እንጂ፣ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ አይደለችም”

ጽዮን ግርማ (የአዲስ አድማስ ጋዜጣ አዘጋጅ)

W/t Birtukanየአዲስ አድማስ ጋዜጣ አዘጋጅ የሆነችው ጋዜጠኛ ጽዮን ግርማ የወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ከእስር በተፈታችበት ዕለት ከቃሊቲ እስር ቤት ጀምሮ ፈረንሣይ በሚገኘው መኖሪያ ቤትዋ ድረስ የነበረውን ትዕይነት በዚህ ሪፖርቷ ታስቃኘናለች። የአንድነት አመራሮች (እነ ኢ/ር ግዛቸው) እንዲሁም የመርኅ ይከበር አባላት (እነ ፕ/ር መስፍን) በወ/ት ብርቱካን ቤት መገናኘትን፣ የፖለቲከኞቹን አስተያየት፣ የህዝቡንና የአካባቢውን ሰዎች አስተያየት ታስነብበናለች። ወ/ት ብርቱካን ለጠ/ሚ መለስ ዜናዊ የፃፈችውን ደብዳቤ፣ የመንግሥት መገናኛ ብዙኀኑን ዘገባ፣ በተለይም በሰነዱ አንደምታ ላይ እና በ”ይቅርታው” ጉዳይ ላይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፍልስፍና እና የኢንስቲትዩት ኦፍ ሂዩማን ራይት መምህር የሆኑት ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋን አናግራለች። ዶ/ር ዳኛቸው ሰነዱን ከአራት ነጥቦች አንጻር በመመዘን ሰፋ ያለ ትንታኔ ሰጥተዋል። ይህንን ሰፋ ያለ ሪፖርታዥ ታነቡ ዘንድ እንጋብዛለን! … መልካም ንባብ!

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ተፈቱ

Hale & W/t Birtukan

Ethiopia Zare (ረቡዕ መስከረም 26 ቀን 2003 ዓ.ም. October 6, 2010)፦ ላለፉት 647 ቀናት በቃሊቲ እስር ቤት ታስረው የነበሩት ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ዛሬ ረቡዕ መስከረም 26 ቀን 2003 ዓ.ም. (ኦክቶበር 6 ቀን 2010 እ.ኤ.አ.) በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር አምስት ሰዓት አካባቢ መፈታታቸውን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ረቡዕ ይፈታሉ

ከ647 ቀናት እስር በኋላ ከወዳጅ ዘመዶቻቸው ይቀላቀላሉ

W/t Birutkan MidekssaEthiopia Zare (ማክሰኞ መስከረም 25 ቀን 2003 ዓ.ም. October 5, 2010)፦ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ሊቀመንበር የሆኑት ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ነገ ጠዋት ረቡዕ መስከረም 26 ቀን 2003 ዓ.ም. (ኦክቶበር 6 ቀን 2010 እ.ኤ.አ.) እንደሚፈቱ የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለፁ። ለመፈታቱ ምክንያት የሽማግሌዎቹ ቡድን እጅ እንዳለበት ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...