ለኢሳት ሥርጭት የተደረገው የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ ተገለጸ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሰኔ 29 ቀን 2002 ዓ.ም. July 06, 2010)፦ በጥቂት ሀገር ወዳዶች የጋራ ጥረትና ስብስብ ተቋቁሞ በኢትዮጵያና በሌሎች የዓለም ክፍሎች መሠራጨት የጀመረውን የኢትዮጵያ ሳይተላይት ቴሌቪዥን ጣቢያ ለመርዳት በስዊድን መዲና ስቶክሆልም ከተማ የገንዘብ ማሰባሰቢያ ዝግጅት መደረጉ ተገለጸ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያዊያን በቶሮንቶ መለስን ተቃውመው ለመሰለፍ እየተሰናዱ ነው

ከዋሽንግተን ዲሲና ከቫንኩቨር ድረስ ኢትዮጵያዊያን እየገቡ ነው

ተክለሚካኤል አበበ-ከቶሮንቶ

እንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠርኸ ከጁን 26 እስከ ጁን 27 በሚካሄደው የጂ 20 ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ ይመጣል ተብሎ የሚጠበቀውን አቶ መለስ ዜናዊና ተከታዮቹን ለመቃወም ከፍተኛ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንና ከሰሜን አሜሪካ የተለያዩ ከተሞች አያሌ ኢትዮጵያዊያን ወደ ቶሮንቶ ይገባሉ ብለው እንደሚጠብቁ አዘጋጆቹ ገለጹ።

 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከሁለት ሺህ በላይ ተፈናቃይ ነዋሪዎች ሃያ እና አስር ሺህ ብር ተጠየቁ

Ethiopia Zare (ሰኞ ሰኔ 14 ቀን 2002 ዓ.ም. June 21, 2010)፦ በአዲስ አበባ ከአራት ኪሎ ጀምሮ እስከ ሁለተኛ ፖሊስ ጣቢያ አካባቢ ያሉ ቤቶች እንዲፈርሱ ተወስኖ፤ መሬቱ ለግል ባለሀብቶች መሸጡ ታወቀ። ተፈናቃዮቹ ከአቅማቸው በላይ ገንዘብ ከፍለው ኮንደሚንየም ቤቶች ውስጥ እንዲገቡ ተጠየቁ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዋሽንግተን ዲሲው ሠልፍ የተሳካ እንደነበር ተገለፀ

March for freedom, Washington DC June14, 2010Ethiopia Zare (ሐሙስ ሰኔ 10 ቀን 2002 ዓ.ም. June 17, 2010) ”ማርች ፎር ፍሪደም” በዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ መዲና ዋሽንግተን ዲሲ በኋይት ሐውስ እና በአሜሪካን የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ፊት ለፊት በጠራው ሠልፍ ላይ በርካታ ኢትዮጵያውያን ተገኝተው፤ የ2002ቱን ምርጫ ኢህአዲግ ማጭበርበሩን በመቃወም የአሜሪካ መንግሥት ኢትዮጵያን አስመልክቶ የሚከተለውን ፖሊሲ እንዲቀይር ጠየቁ። ሠለፉ የተሳካ እንደነበር አዘጋጆቹ ለኢትዮጵያ ዛሬ ገለፁ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

በቦሌ አየር ማረፊያ በሁለት ተጠርጣሪዎች ምክንያት በረራ እንዲዘገይ ተደረገ

Ethiopia Zare (ረቡዕ ሰኔ 9 ቀን 2002 ዓ.ም. June 16, 2010) ባለፈው ሣምንት ማክሰኞ ከአዲስ አበባ ቦሌ አየር ማረፊያ ወደ ቴልሰቪቭ ከምሽቱ 4 ሰዓት ከ35 ላይ ይበር የነበረ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ለአርባ አምስት ደቂቃ ያህል እንዲዘገይ ተደረገ። ይህም የሆነው በደህንነት ሰዎች የተጠረጠሩ ሁለት ተሳፋሪዎችን ተጨማሪ ፍተሻ ሲደረግላቸው መሆኑ ታወቀ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለዓለም ዋንጫ ደ.አፍሪካ ለመሄድ 50 ሺህ ብር የከፈሉ ታገዱ

Ethiopia Zare (ረቡዕ ሰኔ 9 ቀን 2002 ዓ.ም. June 16, 2010) በደቡብ አፍሪካ የሚካሄደውን የ19ኛውን የዓለም ዋንጫ ውድድሮች ለማየት ከኢትዮጵያ ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመሄድ 50 ሺህ ብር የከፈሉ 550 ሰዎች ፈቃድ ተከለከሉ። ያስያዙት ገንዘብ አልተመለሰላቸውም። ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ በረከት ስምዖን በአል ጀዚራ ተፋጠጡ

  • ”እንዲህ ያለ የምርጫ ውጤት በአምባገነኖች ብቻ የሚካሄድ ነው፤ ውጤቱ በሠላማዊ ትግል የሚያምኑትን ሲያኮማሽሽ፣ በትጥቅ ትግል የሚያምኑትን ያበረታታል፤ በዚህም ምክንያት ጦርነት በአካባቢው ቢጀመር ለዓለምም ሆነ ለአካባቢው ከፍተኛ የፀጥታ ችግር ሊያስከትል ይችላል” አቶ ጀዋር መሐመድ (ተመራማሪ)
  • ”ህዝቡ መርጦናል” አቶ በረከት ስምዖን
  • ”መራጮች ወደ ምርጫ ሲሄዱ ከፍተኛ ጥልቀት ባለው ፍርሃት ተሸብበው እንደነበር ለመገመት አያስቸግርም” ሌስሊ ሌፍኮ (ኒዩማን ራይትስ ዎች)

Ethiopia Zare (ሐሙስ ግንቦት 19 ቀን 2002 ዓ.ም. May 27, 2010)፦ ዛሬ የአል ጀዚራ እንግሊዝኛ ቴሌቭዥን ጣቢያ የአቶ መለስ ዜናዊን ቀኝ እጅና የመንግሥት የኮምዩኒኬሽን ሚኒስትር የሆኑትን አቶ በረከትን፣ በግል ተመራማሪና በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ለአል ጀዚራ አስተያየት በመስጠት የሚታወቁት አቶ ጀዋር መሐመድን ከዋሽንግተን፣ እንዲሁም ከሂዩማን ራይትስ ዎች ሌስሊ ሌፍኮን ከዋሽንግተን በ”ኢንሳይድ ስቶሪ” ፕሮግራሙ ባለፈው እሁድ ግንቦት 15 ቀን 2002 ዓ.ም. የተካሄደውን ምርጫ አስመልክቶ አነጋግሯቸዋል። (ሙሉውን ውይይት ለማየትና ለማድመጥ የማጫወቻ ቁልፉን ይጫኑ!)

የአማርኛ እና የኢትዮጵያ ዕሴቶች ማስተማሪያ ዲቪዲ በለንደን ተመረቀ

በ3 ቋንቋዎች የተዘጋጁት ዲቪዲዎችግንቦት 7 2002 ዓ.ም. በለንደን ከተማ በኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ሴንተር ሦስት የአማርኛ እና የኢትዮጵያ ዕሴቶች ማስተማሪያ ዲቪዲ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵውያን እና አፍቃሪ ኢትዮጵያውያን በተገኙብት በደማቅ ሁኔታ ተመረቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ ‘ምርጫ’ እያወዛገበ ነው

“ምርጫው ይደገም” ተቃዋሚዎች

“የምርጫ ሥርዓትን የተከተለ አይደለም” ስቴት ዲፓርትመንት

በግል በብቸኝነት ለፓርላማ ያለፉት ከእግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንትነት ኢህአዲግ በጉልበት ያነሳቸው ዶ/ር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ናቸው

Ethiopia Zare (ረቡዕ ግንቦት 18 ቀን 2002 ዓ.ም. May 26, 2010)፦ በኢትዮጵያ ግንቦት 15 ቀን 2002 ዓ.ም. በተካሄደው ‘ምርጫ’ ገዥው ፓርቲ በቅድመ ምርጫ ቆጠራ ማሸነፉን ካወጀ ወዲህ በተቃዋሚዎች፣ በሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችና በአውሮፓ ታዛቢዎች ከፍተኛ ተቃውሞ እየገጠመው መሆኑ ተነገረ። የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት መግለጫ አውጥቷል። ሙሉውን አስነብበኝ ...