አብን በአማራ ላይ የተቃጡት ጥቃቶች ዳግም እንዳይፈጸሙ ማረጋገጥ ያስፈልጋል አለ

National Movement of Amhara (NAMA) and Prosperity party

የአማራ ብልጽግና ፓርቲም መግለጫ አውጥቷል

ኢዛ (ረቡዕ ሚያዝያ ፲፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 21, 2021)፦ በአማራ ሕዝብ ላይ የተጋረጠው አደጋ ሥርዓትና መዋቅር ሠራሽ በመኾኑ እና የሕዝባችን ትግል የሕልውና ትግል እንደመኾኑ መጠን፤ በሕልውናው ላይ በእቅድና በቅንብር የተከፈቱት ጥቃቶች ዳግም እንዳይፈጸሙ የማረጋገጥ ግቡን እውን ማድረግ አለበት ሲል አብን አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአማራ ክልል ከሰልፍ ያለፈ መፍትሔ ያስፈልጋል አለ

ግዛቸው ሙሉነህ

በአራቱም አቅጣጫ ጥቃት ለመፈጸም ፍላጐት መኖሩንም አስታወቀ
የአንድነት ጥሪ አስተላልፏል

ኢዛ (ረቡዕ ሚያዝያ ፲፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 21, 2021)፦ ጠላቶቻችን በአማራ ላይ በአራቱም አቅጣጫ ለመፈጸም ፍላጐት ያላቸው በመኾኑ፤ ከሰልፍ የዘለለ መፍትሔ እንደሚያስፈልግ የአማራ ክልል አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢሰመጉ የአገሪቱ ሁኔታ በእጅጉ እንዳሳሰበው አስታወቀ

Ethiopian Human Rights Council

መንግሥት በሕገወጥ መንገድ ታጥቆ የንጹሐንን ሕይወት እየቀጠፈ ባለው ቡድን ላይ ሕጋዊ፣ አስቸኳይ እና የማያዳግም እርምጃ እንዲወስድ ኢሰመጉ ጠይቋል

ኢዛ (ረቡዕ ሚያዝያ ፲፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 21, 2021)፦ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ አቅጣጫዎች እየተፈጸመ ያለው የሰዎች ሞት፣ አካል መጉደል፣ መፈናቀል እና በአጠቃላይ የሰብአዊ መብቶች ዋስትና ያጡባት አገር መኾኗን በመጥቀስ፤ በአገሪቱ ላይ የተደቀነው ችግር በእጅጉ እንዳሳሰበው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) ገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአማራ ክልል ተቃውሞው አሁንም እየተሰማ ነው

“አማራን መግደልና ማሳደድ ይቁም!”

አጣየ ከተማ በመውደሟ ነዋሪው በድንኳን እየገባ ነው
ሰልፎቹ ሰላማዊ ቢኾኑም አንዳንድ ያልተገቡ ሁኔታዎች መታየታቸውን የአማራ ክልል ኃላፊ ገለጹ

ኢዛ (ረቡዕ ሚያዝያ ፲፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 21, 2021)፦ ከሚያዝያ 11 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ በአማራ ክልል የተካሔዱ ሰልፎች መንግሥት የዜጐችን ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲያስጠብቅና በዘርና በማንነት ላይ ትኩረት ያደረጉ ጥቃቶች እንዲቆሙ መልእክት የተላለፈበት መኾኑን የአማራ ክልል ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአማራ ክልል የተቃውሞ ሰልፎች ቀጥለዋል

Protest in Amhara region

"አማራን ማሳደድ ይቁም! ሕጻናትን መግደል እና ከተማ ማፍረስ ጀግንነት አይደለም!”

ኢዛ (ማክሰኞ ሚያዝያ ፲፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 20, 2021)፦ በአማራ ላይ ያነጣጠሩ ዘር ተኮር ጥቃቶች እንዲቆሙ እና መንግሥት እነዚህን ጥቃቶች እንዲያስቆም አጥብቀው የጠየቁ ሰላማዊ ሰልፎች በባሕር ዳር፣ በደብረ ማርቆስ፣ በወልዲያ እና በተለያዩ የአማራ ክልል ከተሞች ተካሔዱ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ምርጫ ቦርድ በአዲስ አበባ እና በኦሮሚያ ተጨማሪ ንዑስ ጣቢያዎችን ከፈተ

Ethiopian Election 2021

በአንድ የምርጫ ጣቢያ መመዝገብም ኾነ መምረጥ የሚችለው ሰው ቁጥር 1,500 ብቻ ነው

ኢዛ (ሰኞ ሚያዝያ ፲፩ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 19, 2021)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአዲስ አበባ እና ኦሮሚያ ተጨማሪ 28 ንዑስ የምርጫ ጣቢያዎችን መክፈቱን አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና በብልጽግና ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ እየተሰማ ነው

የአማራ ክልል ተቃውሞ

በኢትዮጵያ ተደጋግሞ የተከሰተውና በተለይም የዘር ጥቃት ጭፍጨፋዎች ልክ አጣ ያሉ ወገኖች “አሁንስ በዛ!” በማለት ድምፃቸውን በአደባባይ ማሰማት ጀምረዋል

ሪፖርታዥ ኢዛ (ሰኞ ሚያዝያ ፲፩ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 19, 2021)፦ በሰሜን ሸዋ እና በአጣየ አካባቢ የደረሰው ጥፋትና ውድመት እስካሁን በውል ያልታወቁ ሰዎችን ሕይወት ሲያጠፋ፤ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በተለይ በአጣየ የዜጐች ቤት እና ንብረት በእሳት ተበልቷል። በለስ ቀንቷቸው ሕይወታቸውን ለማዳን በእግርና በተሽከርካሪዎች ተጭነው የወደመ ቤታቸውን አመድ እየተረማመዱ በገዛ አገራቸው ለመሰደድ ግድ ኾኖባቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢስት አፍሪካ ሆልዲንግ ተጨማሪ የሲሚንቶ ፋብሪካ ሊገነባ ነው

Dire Dawa, National Cement Share Company

የአካባቢ አገሮችን ገበያም ታሳቢ አድርጓል

ኢዛ (ሰኞ ሚያዝያ ፲፩ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 19, 2021)፦ ኢስት አፍሪካ ሆልዲንግ በድሬ ዳዋ ከተማ ከ350 ሚሊዮን ዶላር በላይ ወጪ የሚጠይቀውን አዲስ የሲሚንቶ እና የአርማታ ብረት ፋብሪካ ግንባታ ለመጀመር የመሠረት ድንጋይ አስቀምጧል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የባንክ መመሥረቻ ከ500 ሚሊዮን ወደ አምስት ቢሊዮን ብር አደገ

National Bank of Ethiopia

በሥራ ላይ ካሉት 16 የግል ባንኮች አንዱ ብቻ ነው ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ የተከፈለ ካፒታል ያለው

ኢዛ (ሐሙስ ሚያዝያ ፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 17, 2021)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከዚህ በኋላ ባንክ ለማቋቋም የሚጠየቀውን የካፒታል መጠን አምስት ቢሊዮን ብር ማድረሱን አስታውቋል። በሥራ ላይ ካሉት 16 የግል ባንኮች አንዱ ብቻ ነው ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ የተከፈለ ካፒታል ያለው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መሠረታዊ የምግብ ፍጆታዎች በፍራንኮ ቫሉታ እንዲገቡ ተፈቀደ

ዘይት፣ ስንዴ፣ ስኳር፣ የሕጻናት ወተት እና ሩዝ

የውጭ ምንዛሪ ፈቃድ አይጠየቅም

ኢዛ (ሐሙስ ሚያዝያ ፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 15, 2021)፦ በአሁኑ ጊዜ የሚታየውን የሸቀጦች ዋጋ ንረት እና አቅርቦት ለመቅረፍ መሠረታዊ የምግብ ሸቀጦች የውጭ ምንዛሪ ፈቃድ ሳይጠየቅ በፍራንኮ ቫሉታ እንዲገቡ ተወሰነ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ