“ኢህአዴግ ራሱን ብቻ ለመጪው ምርጫ እያዘጋጀ ነው” የምክክር መድረክ

Ethiopia Zare (እሁድ ጥቅምት 16 ቀን 2001 ዓ.ም. October 26, 2008)፦ የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ጥረት የማዕዘን ደንጋይ የሆኑ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከገዥው ፓርቲ ጋር በ1998 ዓ.ም. የጀመሩት ውይይት ተቋርጦ “ገዢው ፓርቲ ራሱን ብቻ ለመጪው ምርጫ እያዘጋጀ ነው” ሲል መድረክ ለዲሞክራሲያዊ ምክክር በኢትዮጵያ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ 27 ሚሊዮን ዶላር ተጭበረበረ

Ethiopia Zare (እሁድ ጥቅምት 16 ቀን 2001 ዓ.ም. October 26, 2008)፦ በዚህ ሣምንት ኒውዮርክ (አሜሪካ) ከሚገኘው ሲቲ ባንክ ውስጥ ገንዘብነቱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሆነ 27 ሚሊዮን ዶላር ተጭበረበረ። ገንዘቡን ሲያጭበረብሩ የተያዙት ናይጄሪያውያን በቁጥጥር ስር ውለዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሁለቱ ጋዜጠኞች ክስ ሳይመሰረትባቸው ተፈቱ

Ethiopia Zare (ዓርብ ጥቅምት 14 ቀን 2001 ዓ.ም. October 24, 2008)፦ ከረቡዕ ጀምሮ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ቁጥጥር ስር የነበሩት ጋዜጠኛ ሀብቴ ታደሰ እና ጋዜጠኞ አጥናፉ አለማየሁ ምንም አይነት ክስ ሳይመሰረትባቸው ዛሬ ማምሻውን መለቀቃቸውን ከአዲስ አበባ የኢትዮጵያ ዛሬ ሪፖርተር ዘገበ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለኢትዮጵያውን አትሌቶች ድምፅ ይስጡ!

ለ2008 የዓለም አትሌት ምርጫ ሦስት ኢትዮጵያውያን ታጭተዋል

Athlete Haile GebreselaseAthlete Kenenisa BekeleAthlete Tirunesh DibabaEthiopia Zare (ዓርብ ጥቅምት 14 ቀን 2001 ዓ.ም. October 24, 2008)፦ በያዝነው 2008 እ.ኤ.አ. በሞናኮ በሚዘጋጀው የዓለም የ2008 አትሌትን ለመምረጥ በኢንተርኔት የድምፅ አሰጣጥ እየተካሄደ ሲሆን፣ ለዚህ ከታጩት 20 የዓለም ምርጥ አትሌቶች ውስጥ ሦስቱ ኢትዮጵያውያን ናቸው። እርስዎም ድምፅ በመስጠቱ መሳተፍ ይችላሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዳኛ የአባት ስም ስህተት እስከ ሦስት ዓመት የሚያስቀጣ ክስ አስመሰረተ

አንዷ ጋዜጠኛ ክስ ተመስርቶባት በዋስ ስትፈታ፣ ሁለቱ ታስረው አደሩ

Habte Tadesse, journalist, dupty editor-in-cheif of Enbilta weekly Amharic newspaper

ጋዜጠኛ ሀብቴ ታደሰ

Atenafu Alemayehu, journalist, editor of Enbilta weekly Amharic newspaper

ጋዜጠኛ አጥናፉ አለማየሁ

Ethiopia Zare (ኀሙስ ጥቅምት 13 ቀን 2001 ዓ.ም. October 23, 2008)፦ የቴዲ አፍሮን ክስ የሚያስችሉትን ዳኛ የአባት ሥም በስህተት ያተመው የእንቢልታ ጋዜጣ ሦስት አዘጋጆች በዛሬው ዕለት ችሎት ቀርበው አሣታሚና ዋና አዘጋጅዋ ጽዮን ግርማ እስከ ሦስት ዓመት ሊያስቀጣ በሚችል ክስ ተመስርቶባት በዋስ ስትለቀቅ፤ የሁለቱን አዘጋጆች ጉዳይ ዓቃቤ ሕግ ክሴን አላጠናቀቅሁም በማለቱ ታስረው እንዲያድሩ ተደረገ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በቫንኩቨር የቅድስት ማርያም ችሎት ቀጥሏል

ሁለተኛውና ዋና ፀሐፊው አቶ ተክላይ ዛሬ ቃላቸውን ሰጥተዋል

ዳኛው ገንዘቡ እንዳይባክን በሽምግልና እንዲፈታ ጠየቁ

Ethiopia Zare (ኀሙስ ጥቅምት 13 ቀን 2001 ዓ.ም. October 23, 2008)፦ በቫንኩቨር ከተማ በብሪቲሽ ኮሎምቢያ ጠቅላይ ፍ/ቤት የተሰየመው ችሎት በቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ጉዳይ ላይ ዛሬም ቀጥሎ የዋለ ሲሆን፣ በዛሬው ዕለት ሁለተኛው ተከሳሽና ምስክር አቶ ተክላይ ጸጋዬ ምስክርነት ሲሰጡና መስቀለኛ ጥያቄ ሲጠየቁ ውለዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በቴዲ አፍሮ ችሎት ዳኛ ስም ስህተት ሦስት ጋዜጠኞች ታስረው አደሩ

(ተጨማሪ ዘገባ)  

Tsion Girma, journalist, Publisher & editor-in-chief of Enbilta weekly Amharic newspaper
ጋዜጠኛ ጽዮን ግርማ
Habte Tadesse, journalist, dupty editor-in-chief of Enbilta weekly Amharic newspaper
ጋዜጠኛ ሀብቴ ታደሰ

ከሳሻቸው ፍትህ ሚኒስቴር ነው 

ፍርድ ቤት ቅጽር ግቢ ውስጥ ታስረው ቢውሉም ችሎት አልቀረቡም

Ethiopia Zare (ረቡዕ ጥቅምት 12 ቀን 2001 ዓ.ም. October 22, 2008)፦ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በስልክ የጠራቸውን ሦስት ጋዜጠኞችን ቃላቸውን ተቀብሎ ልደታ በሚገኘው የፌዴራሉ ፍርድ ቤት ፈጣን ችሎት ሊያቀርባቸው የሞከረ ሲሆን፣ ዓቃቤ ሕግ ክሱን ሊያቀርብ ባለመቻሉ ሦስቱም ጋዜጠኞች በተለምዶ ሦስተኛ ተብሎ በሚጠራው ፖሊስ ጣቢያ ታስረው እንዲያድሩ መደረጉን ከአዲስ አበባ የደረሰን ዘገባ አስረዳ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የቴዲ አፍሮን ችሎት የሚያዩትን ዳኛ ስም የተሳሳቱ ሦስት ጋዜጠኞች ታሰሩ

ጋዜጠኞቹ የእንቢልታ አሣታሚና ዋና አዘጋጅ፣ ምክትል ዋና አዘጋጅ እና አዘጋጅ ናቸው

Ethiopia Zare (ረቡዕ ጥቅምት 12 ቀን 2001 ዓ.ም. October 22, 2008)፦ እንቢልታ ጋዜጣ የቴዲ አፍሮን ዘገባ በጋዜጣው ላይ ሲያስነብብ የዳኛውን የአባት ስም በመሳሳቱ የጋዜጣው አሣታሚና ዋና አዘጋጅ ጽዮን ግርማ፣ ምክትል አዘጋጁ ሀብቴ ታደሰ እና አዘጋጁ አጥናፉ ዓለማየሁ ዛሬ ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮምሽን በእስር ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ድራማ በብሪቲሽ ኮሎምቢያ (ቫንኩቨር) ጠቅላይ ፍ/ቤት

ተከሳሾች ምስክሮቻቸውን ማቅረብ ጀመሩ

የቅድስት ምርያም ቤ/ክርስቲያን የችሎት ውሎ

Ethiopia Zare (ረቡዕ ጥቅምት 12 ቀን 2001 ዓ.ም. October 22, 2008)፦ ባለፈው ሣምንት በቫንኩቨር ከተማ፣ በብሪቲሽ ኮሎምቢያ ጠቅላይ ፍ/ቤት የቫንኩቨር ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያንን መሰረት ያደረገ ክስ መሰማቱን መዘገባችን ይታወሳል። ችሎቱ በዚህ ሣምንትም ቀጥሎ ውሎ በትናንትናው ዕለት የተከሳሾች ዋንኛ ምስክርና በ1995 ዓ.ም. በአቡነ መርቆሪዎስ በሚመራው ሲኖዶስ የተቋቋመችውንና ለአሥር ዓመትም በዚያ መልኩ የቆየችውን ቤ/ክ በአዲስ ሕግና መተዳደሪያ ደንብ ያለህዝቡ ፈቃድ ወደ አባ ጳውሎስ እንዲዞሩ ወይንም እነሱ እንደሚሉት ገለልተኛ እንድትሆን ካደረጉት አምስት የቦርድ ዳይሬክተሮች መካከል አቶ አበበ ንስሬ ምስክርነት ሲሰጥ ውሏል። ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንድነት በየክልሉ ከተሞች ጽ/ቤት ለመክፈት ተንቀሳቀሰ

የመጀመሪያው ቡድን ዛሬ ወደ ደሴ ይጓዛል

Ethiopia Zare (ሰኞ ጥቅምት 10 ቀን 2001 ዓ.ም. October 20, 2008)፦ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ሕጋዊ ፈቃዱን ካገኘ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በየክልሉ ከተሞች ጽ/ቤቶችን ለመክፈትና ከህዝብ ጋር ውይይት ለማድረግ በወ/ት ብርቱካን የሚመራው የልዑካን ቡድን ዛሬ እንቅስቃሴ መጀመሩን የድርጅቱ ቃል አቀባይ ዶ/ር ኃይሉ አርኣያ በተለይ ለኢትዮጵያ ዛሬ አረጋገጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...