38 የፓርላማ አባላት በአንድነት ስም ለመንቀሳቀስ ጥያቄ አቀረቡ

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ጥቅምት ፩-1 ቀን ፳፻፩-2001 ዓ.ም. October 11, 2008)፦ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ ያላቸው 38 የአንድነት ፓርቲ መሥራች አባላት፣ በፓርላማ ውስጥ በአንድነት ፓርቲ ስም ለመንቀሳቀስ ጥያቄ አቀረቡ። አባላቱ ጥያቄውን ያቀረቡት መስከረም 28 ቀን 2001 ዓ.ም. ለአፈ-ጉባዔው ጽሕፈት ቤት ባስገቡት ደብዳቤ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኤርትራ ሕፃናት ለከፋ የምግብ እጥረት እየተጋለጡ ነው

ለኤርትራ ዕርዳታ ሁለት ሚሊየን ዶላር ያስፈልጋል

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ጥቅምት ፩-1 ቀን ፳፻፩-2001 ዓ.ም. October 11, 2008)፦ የተባበሩት መንግሥታት የሕፃናት ፈንድ ዩኒሴፍ እንዳስታወቀው፣ በኤርትራ በርካታ አካባቢዎች ሕፃናት ለከፋ የምግብ እጥረት እየተጋለጡ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቴዲ አፍሮ ዛሬ የተከሳሽ የምስክረነት ቃሉን ሰጠ

የቴዲ አፍሮ ችሎት ውሎ

ጠበቆች ከቆጠሯቸው 14 ምስክሮች 12ቱ መጥሪያ ደርሷቸዋል፤ 7ቱ ዛሬ መሰከሩ

የሰባቱንም የምስክርነት ቃል ይዘናል

የኩባዊው የአስከሬን መርማሪ በጠበቆቹ ለምስክርነት መጠራት አከራከረ

Teddy Afro

 

Ethiopia Zare (ኀሙስ መስከረም ፳፱-29 ቀን ፳፻፩-2001 ዓ.ም. October 9, 2008)፦ ዛሬ ኀሙስ መስከረም 29 እንደተለመደው በጠዋቱ ችሎት ጉዳዩ ይታያል ብሎ የገመተ ቁጥሩን ለመገመት የሚያዳግት በርካታ ችሎት ተከታታይ ገና ከጠዋቱ ነበር፣ የፌደራሉ ፍርድ ቤት ሁለቱ መግቢያዎች ላይ እየተጋፋ የተሰለፈው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቴዲ አፍሮ ዛሬ ፍርድ ቤት ይቀርባል

Teddy Afroላለፉት 176 ቀናት በእስር ቆይቷል

Ethiopia Zare (ኀሙስ መስከረም ፳፱-29 ቀን ፳፻፩-2001 ዓ.ም. October 9, 2008)፦ ባለፈው ዓመት ሐምሌ 14 ቀን 2000 ዓ.ም. ለመጨረሻ ጊዜ ቀርቦ የነበረው አርቲስት ቴዎድሮስ ካሣሁን (ቴዲ አፍሮ) ከ75 ቀናት በኋላ ዛሬ (ኀሙስ መስከረም 29) ለመጀመሪያ ጊዜ በያዝነው አዲስ ዓመት ፍርድ ቤት ይቀርባል። ቴዲ አፍሮ ላለፉት አምስት ወራት ከ26 ቀናት በድምሩ 176 ቀናት በእስር ላይ ቆይቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አስገራሚው የሕፃኗ ቀዶ ጥገና በአዲስ አበባ

Tarikuwa Boche, age 2Ethiopia Zare (ረቡዕ መስከረም ፳፰-28 ቀን ፳፻፩-2001 ዓ.ም. October 8, 2008)፦ ወ/ሮ መስከረም አሰግድ ይባላሉ። ጭድና ጭቃ በመቀላቀል ውበት ያላቸው የአርት ሥራዎችን በቤቱ ውስጥ ከሚሠራው አርቲስት ኤሊያስ ጋር ሠንበሌጥ ሣር ፍለጋ ከአዲስ አበባ በስተምስራቅ 47 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ደብረዘይት (ቢሾፍቱ) ከተማ ቱሉ ኮርማ ተራራ በከታ ወረገኑ ገጠር ገበሬ ማኅበር ያመራሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢቲኤን በብሮድባንድ ሥርጭቱን በመላው ዓለም ሊጀምር ነው

Ethiopia Zare (ማክሰኞ መስከረም ፳፯-27 ቀን ፳፻፩-2001 ዓ.ም. October 7, 2008)፦ በዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ የሚገኘው የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ኔትዎርክ (ኢ.ቲ.ኤን.) በአዲስ ቴክኖሎጂ ሥርጭቱን በመላው ዓለም የብሮድባንድ ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በሙሉ ለማዳረስ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ለኢትዮጵያ ዛሬ በላከው መግለጫ ገለፀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአሜሪካ የጦር ዕዝ በሶማሊያ የባህር ላይ ወንበዴዎች

U.S. Navy destroyer USS Howard, left, and the Russian missile frigate Neustrashimy responded to the Somalia coast in response to a pirate hijacking.
“ዩ.ኤስ.ኤስ. ሐዋርድ” የተሰኘችው የዩናይትድ ስቴትስ የአሜሪካ ባህር ኃይል የጦር መርከብ (በግራ)፣ የሩሲያ “ኑስትራሺሚ” የተሰኘችው ሚሳይል ተሸካሚ የጦር መርከብ (በቀኝ) (ፎቶ AP)
አሜሪካ በአፍሪካ የጦር ዕዝ እንዲኖራት ፍላጎት እንዳላት ካስታወቀች ዓመታት ተቆጥረዋል። አሁንም ፍላጎቷ በአብዛኛዎቹ አፍሪካውያን እንደ ትልቅ ስጋት እየታየ ነው። በአፍሪካ የአሜሪካ ወታደራዊ ዕዝ (Africom) አዛዥ ጄኔራል ዊልያም ዋርድ እንደሚገልፁት የአሜሪካ የጦር ዕዝ በአፍሪካ መቋቋሙ ድብቅ አጀንዳ የለውም፤ አሜሪካ በአፍሪካ የተፈጥሮ ሀብትን በተለይም ዘይትን ለመመዝበር ፍላጎት አላት የሚለውም የተዛባ ነው ብለውታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ12ኛ መልቀቂያ ፈተና የወደቁ ዲቪ ማመልከት አይችሉም

ዲቪ 2010 ተጀምሯል

Ethiopia Zare (ሰኞ መስከረም ፳፮-26 ቀን ፳፻፩-2001 ዓ.ም. October 6, 2008)፦ የአሜሪካን ኤምባሲ እ.ኤ.አ. የ2010 ዓ.ም. የዲቪ ሎተሪ አመልካቾች ማመልከቻቸውን ከኦክቶበር 1 ቀን 2008 ዓ.ም. (መስከረም 21 ቀን 2001 ዓ.ም.) ጀምሮ ማቅረብ የሚችሉ መሆኑን አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሥልጣናቸውን በገዛ ፈቃዳቸው የሚለቁ የአፍሪካ መሪዎች 5 ሚሊዮን ዶላር ይሸለማሉ

ሞ ኢብራሂም የአፍሪካን የመልካም አስተዳደር ሪፖርት ይፋ ያደርጋሉ

Dr. Mo IbrahimEthiopia Zare (እሁድ መስከረም ፳፭-25 ቀን ፳፻፩-2001 ዓ.ም. October 5, 2008)፦ የሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽን ነገ ሰኞ መስከረም 26 ቀን 2001 ዓ.ም. የአፍሪካ ሀገሮችን የመልካም አስተዳደር ሪፖርት በአዲስ አበባ ይፋ ሊያደርግ ነው። 

ሙሉውን አስነብበኝ ...