የኢ.ቲ.ቪን አሠራር የተቃወሙ ጋዜጠኞች ለጠ/ሚሩ አቤቱታ አቀረቡ

Ethiopia Zare (ቅዳሜ መስከረም ፲፯ /17 ቀን ፳፻፩/2001 ዓ.ም. September 27, 2008)፦ የኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቭዥን ድርጅት የቴሌቭዥን ዘርፍ፣ አዲስ በጀመረው የሰዓት ጭማሪና በጣቢያው ስር ይተዳደሩ የነበሩ የኦሮምኛና የትግርኛ ፕሮግራሞች ወደ ክልሎቻቸው እንዲሄዱ መደረጉን በመቃወም፣ የኦሮምኛ ፕሮግራም ክፍል ሠራተኞች ለጠ/ሚ መለስ እና ለተለያዩ ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቶች ደብዳቤ አስገቡ። ሠራተኞቹ ጣቢያው ከእነርሱ ጋር ውይይትና አስፈላጊ ዝግጅት ሳያደርግ የጀመረው እንደሆነ ሲገልጹ፣ የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን በበኩሉ ፕሮግራሙን የማሳደግና የማስፋፋት ሥራ እየሠራሁ ነው ብሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ በ10 ምርጦች

Ethiopia Zare (ቅዳሜ መስከረም ፲፯ /17 ቀን ፳፻፩/2001 ዓ.ም. September 27, 2008)፦ ኢትዮጵያን በመጥፎም ሆነ በበጐ ጐን ከዓለም አስር ሀገራት ተርታ የሚያሰልፏት ሩሴል አቮ የተባሉ ደራሲ (Top 10 of everything 2009) በሚል መጽሐፋቸው ያሰፈሯቸው ጉዳዮች አንዳንዶቹ የሚታወቁ ሌሎቹ ደግሞ ፈጽሞ የማይታወቁ አስገራሚ ነገሮች ናቸው። ለምሣሌ የዓለማችን ዋነኛ ሞቃት ሥፍራ ዳሎል በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፣ 94.3 ዲግሪ ፋራናይት ወይም 34.6 ዲግሪ ሴንቲግሬድ ሙቀት እንዳለው በመጽሐፉ ላይ ተጠቅሷል፤ ከዳሎል ቀጥሎ በሞቃታማነቱ የተጠቀሰው በኤርትራ የሚገኘው አሰብ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የደመራ በዓል ለሁለተኛ ጊዜ በስዊድን ተከበረ

Demera, Stockholm 2008,09,26Ethiopia Zare (ዓርብ መስከረም ፲፮ (16) ቀን ፳፻፩ (2001) ዓ.ም. September 26, 2008)፦ በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም ደብረሠላም መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን የደመራ በዓል በደማቅ ሁኔታ አከበረች። ሥነሥርዓቱ አመሻሹ 11፡00 ሰዓት (17፡00) ላይ ተጀምሮ እስከ ምሽቱ 2፡00 ሰዓት (20፡00) የዘለቀ ሲሆን፣ በስቶክሆልምና አካባቢው የሚኖሩ ምዕመናን ተገኝተዋል። 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሉሲ ወደ ሲያትል ትሄዳለች

ጠ/ሚኒስትር መለስ ይጎበኟታል ተባለ

ኢትዮጵያዊያኖች ለተቃውሞ እየተዘጋጁ ነው

Ethiopia Zare (ማክሰኞ መስከረም ፲፫ (13) ቀን ፳፻፩ (2001) ዓ.ም. September 23, 2008)፦ ለጉብኝት በሰሜን አሜሪካ ዋና ዋና ከተሞች በመዘዋወር ላይ የምትገኘው ድንቅነሽ (ሉሲ) ከሂውስተን ወደ ሲያትል-ዋሽንግተን የምታቀና ሲሆን፣ ጠ/ሚኒስትር መለስ ጉብኝቱን ትኩረት ለማሰጠት በስፍራው እንደሚገኙ ያወቁ ኢትዮጵያዊያን ለተቃውሞ ከፍተኛ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች አረጋገጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የጋዜጣና የመጽሔት ፈቃድ መስጠት ተቋረጠ

አዲሱ ሕግ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ እስኪወጣ እየተጠበቀ ነው

Ethiopia Zare (ቅዳሜ መስከረም ፲ (10) ቀን ፳፻፩ (2001) ዓ.ም. September 20, 2008)፦ በማስታወቂያ ሚኒስቴር የፕሬስ ፈቃድና የሚዲያ ግንኙነት አንድ ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ይሰጥ የነበረውን የፕሬስ ሥራ የብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ አዲሱ ዐዋጅ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ እስኪወጣ ድረስ መስጠት አቆመ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢህአዴግ ከ36 የሥራ አስፈፃሚ አባላቱ አንዲት ሴት ብቻ መርጧል

Ethiopia Zare (ቅዳሜ መስከረም ፲ (10) ቀን ፳፻፩ (2001) ዓ.ም. September 20, 2008)፦ ሰሞኑን በሐዋሳ በተካሄደው 7ኛው የኢህአዴግ ጉባዔ ለድርጅቱ ሥራ አስፈፃሚነት ከመረጣቸው 36 አባላት መካከል አንድ ሴት ብቻ መምረጡ ፓርቲው ለሴቶች ተሳትፎ የሰጠውን አነስተኛ ግምት እንደሚያሳይ አስተያየት ሰጪዎች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በ7ኛው የኢህአዴግ ጉባዔ

“ሕጉንና ሕገመንግሥቱን አክብረው የሚሠሩ ፓርቲዎች መጥራት ይገባቸዋል”

ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ

“ካሉን 60 ሺህ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች (የተማሩ) አባሎቻችን የተወሰኑት በመታወቂያው ሥራ መፈለጊያና ትምህርት ቤት መግቢያ አድርገውታል፤በቀጣይ የማጥራት ሥራ እንሠራለን”

አቶ በረከት ስምዖን

“በሚቀጥሉት ዓመታት በየዓመቱ 7 ሺህ ዶክተሮችን በማስመረቅ ገበያውን በዶክተሮች ማጥለቅለቅና ተጨማሪ ማበረታቻዎችን በመስጠት ማቆየት ዕቅዳችን ነው”

የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድኃኖም

Ethiopia Zare (ቅዳሜ መስከረም ፲ (10) ቀን ፳፻፩ (2001) ዓ.ም. September 20, 2008)፦ ከሰኞ መስከረም 5 ቀን 2001 ዓ.ም. ጀምሮ በሐዋሳ ከተማ ለሦስት ቀናት በተደረገው 7ኛው የኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባዔ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፖርቲዎችን አስመልክተው ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ እንደገለጹት፣ ሕገመንግሥቱን በማጣቀስ ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች እንዳሉ ገልጸው፣ ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን አክብረው የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች በጣም ጥቂት ናቸው ብለዋል፤ ስለዚህም ሕጉንና ሕገመንግሥቱን አክብረው የሚሠሩ ፓርቲዎች መጥራት ይገባቸዋል ሲሉ ተደምጠዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...